የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w17 ሰኔ ገጽ 32
  • ይህን ያውቁ ኖሯል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይህን ያውቁ ኖሯል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይህን ያውቁ ኖሯል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • ኢየሱስ ነጋዴዎችን ከቤተ መቅደሱ አባረረ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ቤተ መቅደሱ እንደገና ጸዳ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ኢየሱስ ቤተ መቅደሱን አጸዳ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
w17 ሰኔ ገጽ 32
Jኢየሱስ በቤተ መቅደሱ የሚሸጡትንና የሚገዙትን ሁሉ አስወጣ

ይህን ያውቁ ኖሯል?

በኢየሩሳሌም በሚገኘው ቤተ መቅደስ ውስጥ እንስሳት ይሸጡ የነበሩት ሰዎች “ዘራፊዎች” መባላቸው ተገቢ ነው የምንለው ለምንድን ነው?

የማቴዎስ ወንጌል እንዲህ ይላል፦ “ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደሱ ገብቶ በቤተ መቅደሱ የሚሸጡትንና የሚገዙትን ሁሉ አስወጣ፤ የገንዘብ መንዛሪዎችን ጠረጴዛዎችና የርግብ ሻጮችን መቀመጫዎችም ገለባበጠ። እንዲህም አላቸው፦ ‘“ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል” ተብሎ ተጽፏል፤ እናንተ ግን የዘራፊዎች ዋሻ አድርጋችሁታል።’”—ማቴ. 21:12, 13

የአይሁድ የታሪክ መዛግብት እንደሚያሳዩት በቤተ መቅደሱ የነበሩት ነጋዴዎች የእንስሳቱን ዋጋ በጣም በማስወደድ ገዢዎቹን ይበዘብዙ ነበር። ለምሳሌ ያህል፣ ሚሽና የተባለው መጽሐፍ (ኬሪቶት 1:7) በመጀመሪያው መቶ ዘመን መሥዋዕት ሆነው የሚቀርቡ ሁለት ርግቦች ዋጋ አንድ የወርቅ ዲናር ደርሶ እንደነበር ዘግቧል። አንድ የወርቅ ዲናር ከአንድ የጉልበት ሠራተኛ የ25 ቀን ደሞዝ ጋር ተመጣጣኝ ዋጋ ነበረው። ድሆች ርግቦችን ወይም ዋኖሶችን መሥዋዕት አድርገው ማቅረብ ይፈቀድላቸው ነበር፤ ሆኖም የእነዚህ ወፎች ዋጋ እንኳ የማይቀመስ ሆኖ ነበር። (ዘሌ. 1:14፤ 5:7፤ 12:6-8) ስምዖን ቤን ገማልያል የተባለ ረቢ በዚህ ሁኔታ በጣም በመበሳጨቱ አይሁዳውያን ማቅረብ የሚጠበቅባቸው መሥዋዕቶች ቁጥር እንዲቀንስ አደረገ፤ በዚህም ምክንያት የሁለት ርግቦች ዋጋ ወዲያውኑ ቀነሰ።

ከዚህ መመልከት እንደምንችለው በቤተ መቅደሱ የነበሩት ነጋዴዎች ስግብግብና ሕዝቡን የሚበዘብዙ ነበሩ። በመሆኑም ኢየሱስ እነዚህን ነጋዴዎች “ዘራፊዎች” ብሎ መጥራቱ ተገቢ ነው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ