የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp19 ቁጥር 1 ገጽ 15
  • አምላክን ማወቅህ ምን ጥቅም ያስገኝልሃል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አምላክን ማወቅህ ምን ጥቅም ያስገኝልሃል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2019
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ከይሖዋ ጋር ያለህን ወዳጅነት አጠናክር
    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?
  • አምላክን ማወቅ የምትችለው እንዴት ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • አምላክ ከማንም የሚበልጥ ወዳጅ ነው
    የአምላክ ወዳጅ መሆን ትችላለህ!
  • ከዚህ የሚበልጥ አስደሳች ሕይወት የለም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2019
wp19 ቁጥር 1 ገጽ 15
በገነት ውስጥ አስደሳች ሕይወት እየመሩ ያሉ ሰዎች

አምላክን ማወቅህ ምን ጥቅም ያስገኝልሃል?

እስካሁን ባየናቸው ተከታታይ ርዕሶች ላይ ‘አምላክ ማን ነው?’ ለሚለው ጥያቄ ደረጃ በደረጃ መልስ ለማግኘት ሞክረናል። በመጀመሪያ የአምላክ ስም ይሖዋ እንደሆነና ዋነኛ ባሕርይው ፍቅር እንደሆነ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተመልክተናል። ከዚያም ለሰብዓዊ ፍጥረታቱ ሲል ከዚህ በፊት ያደረገውንና ወደፊትም የሚያደርገውን ነገር አይተናል። ይሁንና ስለ አምላክ ማወቅ የሚያስፈልግህ ገና ብዙ ነገር አለ። ሆኖም ‘ስለ አምላክ ማወቄ ምን ጥቅም ያስገኝልኛል?’ ብለህ ታስብ ይሆናል።

ይሖዋ ‘ከፈለግከው እንደሚገኝልህ’ ቃል ገብቷል። (1 ዜና መዋዕል 28:9) አምላክን መፈለግህና እሱን ይበልጥ እያወቅከው መሄድህ የሚያስገኝልህን ግሩም ሽልማት ለማሰብ ሞክር፤ “ከይሖዋ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት” መመሥረት ትችላለህ! (መዝሙር 25:14) እንዲህ ያለ ወዳጅነት መመሥረትህ የሚጠቅምህ እንዴት ነው?

እውነተኛ ደስታ ያስገኝልሃል። ይሖዋ “ደስተኛው አምላክ” ተብሎ ተጠርቷል። (1 ጢሞቴዎስ 1:11) ወደ እሱ ለመቅረብና እሱን ለመምሰል ጥረት ማድረግህ እውነተኛ ደስታ እንዲኖርህ ያደርጋል፤ ይህም ስሜታዊ፣ አእምሯዊና አካላዊ ጥቅም እንድታገኝ ያስችልሃል። (መዝሙር 33:12) በተጨማሪም ጎጂ ከሆነ አኗኗር ስለምትርቅ፣ ጤናማ ልማዶችን ስለምታዳብርና ከሌሎች ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለሚኖርህ በሕይወትህ ደስተኛ ትሆናለህ። በመሆኑም መዝሙራዊው “ወደ አምላክ መቅረብ ይበጀኛል” በማለት የተናገረው ሐሳብ እውነት መሆኑን በገዛ ሕይወትህ ትመለከታለህ።—መዝሙር 73:28

በግለሰብ ደረጃ ትኩረትና እንክብካቤ እንድታገኝ ያስችልሃል። ይሖዋ ለአገልጋዮቹ “ዓይኔን በአንተ ላይ አድርጌ እመክርሃለሁ” በማለት ቃል ገብቶላቸዋል። (መዝሙር 32:8) በመሆኑም ይሖዋ ለአገልጋዮቹ በግለሰብ ደረጃ ትኩረት ይሰጣቸዋል፤ እንዲሁም ለእያንዳንዳቸው የሚያስፈልጋቸውን እንክብካቤ ያደርግላቸዋል። (መዝሙር 139:1, 2) ከይሖዋ ጋር ጥሩ ዝምድና ከመሠረትክ ይሖዋ ምንጊዜም ከጎንህ እንደሚሆን ማስተዋል ትችላለህ።

አስደሳች ተስፋ ይኖርሃል። ይሖዋ አምላክ በዛሬው ጊዜ አስደሳችና እርካታ ያለው ሕይወት እንድትመራ ከማድረግ በተጨማሪ የወደፊቱን ጊዜ በተመለከተ ብሩሕ ተስፋ እንዲኖርህ አድርጓል። (ኢሳይያስ 48:17, 18) መጽሐፍ ቅዱስ “የዘላለም ሕይወት ማግኘት እንዲችሉ ብቸኛው እውነተኛ አምላክ የሆንከውን አንተንና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ አለባቸው” በማለት ይናገራል። (ዮሐንስ 17:3) አምላክ የሚሰጠው ተስፋ፣ ተነዋዋጭ በሆነው በዚህ ዓለም ውስጥ “አስተማማኝና ጽኑ” እንደሆነ መልሕቅ ይሆንልሃል።—ዕብራውያን 6:19

እስካሁን የተመለከትነው፣ አምላክን ይበልጥ ማወቃችንና ከእሱ ጋር የግል ዝምድና መመሥረታችን ከሚያስገኝልን በርካታ ጥቅሞች መካከል ጥቂቶቹን ብቻ ነው። ስለዚህ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የይሖዋ ምሥክሮችን ማነጋገር ወይም jw.org የተባለውን ድረ ገጻችንን መጎብኘት ትችላለህ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ