ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ታኅሣሥ:- ታላቅ ሰው፤ ጥር:- ነቅተህ ጠብቅ! የካቲት:- ወደ ይሖዋ ቅረብ፤ መጋቢት:- ነቅተህ ጠብቅ! የተባለው ብሮሹር የሚበረከት ሲሆን ግለሰቦች ፍላጎት ካሳዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስጀመር ግብ ይዛችሁ እውቀት መጽሐፍን አስተዋውቁ።
◼ ለ2006 የመታሰቢያ በዓል የሚያገለግል የመጋበዣ ወረቀት ጉባኤው በሚመራበት ቋንቋ በቅርቡ ለጉባኤዎች ይላካል።
◼ በ2007 የመታሰቢያው በዓል የሚከበርበት ዕለት ሰኞ፣ ሚያዝያ 2 ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ ይሆናል። ይህ ማስታወቂያ አስቀድሞ የወጣው ወንድሞች ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንዲችሉ ታስቦ ነው።
◼ በዓሉ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ከመሆኑ አኳያ የሽማግሌዎች አካል የመታሰቢያውን ንግግር የሚያቀርበውን ወንድም ሲመድብ ብቃት ያለውን ሽማግሌ ይመርጣል እንጂ በተራ እንዲዳረስ ወይም በየዓመቱ አንድ ሽማግሌ ብቻ እንዲያቀርብ ማድረግ የለበትም። ንግግሩን በሚገባ ማቅረብ የሚችል ቅቡዕ ሽማግሌ ካለ እርሱ ሊመደብ ይገባል።