የካቲት 8 የሚጀምር ሳምንት
የካቲት 8 የሚጀምር ሳምንት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
lv ምዕ. 9 አን. 1-12፤ በገጽ 101 ላይ የሚገኘው ሣጥን
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ መሳፍንት 11-14
ቁ. 1፦ መሳፍንት 13:1-14
ቁ. 2፦ በሉቃስ 16:9-13 ላይ ተመዝግበው ከሚገኙት የኢየሱስ ቃላት ምን እንማራለን?
ቁ. 3፦ በራእይ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሰው ‘የዘላለም ሥቃይ’ ምንድን ነው? (rs ገጽ 172 አን. 4 እስከ ገጽ 173 አን.1)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
10 ደቂቃ፦ በዓላትን አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ መስጠት። በማመራመር መጽሐፍ ገጽ 178 አን. 4 ላይ ከሚጀምረው ንዑስ ርዕስ አንስቶ እስከ ገጽ 180 አን. 2 ድረስ ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ ከአድማጮች ጋር በሚደረግ ውይይት የሚቀርብ። በክልላችሁ ውስጥ የሚገኙት ሰዎች የሚያከብሯቸው በዓላት የትኞቹ ናቸው? አንድን በዓል በተመለከተ ምሥክርነት ለመስጠት አመቺ የሚሆንላችሁ ጊዜና ቦታ መጥቀስ ትችላላችሁ? አንድ ወላጅ፣ ልጁ ‘የፋሲካን በዓል የማታከብረው ለምንድን ነው?’ ተብሎ ሲጠየቅ እንዴት ብሎ መልስ መስጠት እንደሚችል ሲያሠለጥነው የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ አቅርብ።
20 ደቂቃ፦ “የመታሰቢያው በዓል መጋበዣ በዓለም ዙሪያ ይሰራጫል!” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ። አንቀጽ 2ን ከመወያየታችሁ በፊት የመታሰቢያው በዓል መጋበዣ ወረቀት ደርሶ ከሆነ አንድ ቅጂ ለአድማጮች እንዲታደል አድርግ፤ ከዚያም መጋበዣ ወረቀቱ ያለውን የተለያዩ ገጽታዎች አብራራ። አንቀጽ 2ን ከተወያያችሁ በኋላ በመጋበዣ ወረቀቱ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ። ከመታሰቢያው በዓል ጋር በተያያዘ የሚካሄደውን ዘመቻ አስመልክቶ ስለተደረገው ተጨማሪ የመስክ አገልግሎት ስምሪት ዝግጅት ማብራሪያ እንዲሰጥ ለአገልግሎት የበላይ ተመልካቹ ወይም ለሌላ ሽማግሌ ቃለ ምልልስ አድርግለት።