የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • g 4/14 ገጽ 7
  • 1 ሁኔታዎች ይለወጣሉ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • 1 ሁኔታዎች ይለወጣሉ
  • ንቁ!—2014
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሞቼ ብገላገልስ?
    ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 1
  • 4 | ተስፋህ
    ንቁ!—2022
  • ራሴን የማጥፋት ሐሳብ ሲመጣብኝ መጽሐፍ ቅዱስ ሊረዳኝ ይችላል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ለውጥን ማስተናገድ የሚቻለው እንዴት ነው?
    ንቁ!—2016
ለተጨማሪ መረጃ
ንቁ!—2014
g 4/14 ገጽ 7

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | መኖር ምን ዋጋ አለው?

1 ሁኔታዎች ይለወጣሉ

“በየአቅጣጫው ብንደቆስም መፈናፈኛ አናጣም፤ ግራ ብንጋባም መውጫ ቀዳዳ አናጣም።”—2 ቆሮንቶስ 4:8

ራስን ማጥፋት “ጊዜያዊ ለሆነ ችግር ዘላቂ የሆነ መፍትሔ መስጠት” እንደሆነ ተደርጎ ይገለጻል። ለማመን ቢከብድህም እንኳ ማንኛውም ዓይነት አስጨናቂ ሁኔታ ሌላው ቀርቶ ከአንተ ቁጥጥር ውጭ እንደሆነ የሚሰማህም ጭምር ጊዜያዊ ሊሆን ይችላል። እንዲያውም ባልጠበቅከው መንገድ ሊስተካከል ይችላል።—“ሁኔታቸው ተለውጧል” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።

ይህ ባይሆን እንኳ ስለ ነገ ሳትጨነቅ ዛሬ በሚያጋጥሙህ ችግሮች ላይ ብቻ በማተኮር መፍትሔ መፈለግህ የተሻለ ነው። ኢየሱስ “ስለ ነገ ፈጽሞ አትጨነቁ፤ ምክንያቱም ነገ የራሱ የሆኑ የሚያስጨንቁ ነገሮች አሉት። እያንዳንዱ ቀን የራሱ የሆነ በቂ ችግር አለው” ብሏል።—ማቴዎስ 6:34

ይሁንና ሁኔታህ ሊለወጥ የማይችል ቢሆንስ? ለምሳሌ ሥር የሰደደ ሕመም ይኖርብህ ይሆናል። አሊያም ያስጨነቀህ ነገር የትዳር መፍረስ ወይም የቤተሰብህን አባል በሞት እንደማጣት ያለ ልትቀይረው የማትችል ነገር ቢሆንስ?

በዚህ ጊዜም ቢሆን ልትለውጠው የምትችለው ነገር ይኖራል፤ ስለ ሁኔታው ያለህን አመለካከት መለወጥ ትችላለህ። ልትለውጠው የማትችለውን ነገር ተቀብለህ ለመኖር ስትጥር ነገሮችን ይበልጥ አዎንታዊ በሆነ መንገድ ማየት ትጀምራለህ። (ምሳሌ 15:15) በተጨማሪም ሞትን እንደ መፍትሔ ከመቁጠር ይልቅ ሁኔታውን ለመቋቋም የምትችልባቸውን መንገዶች መፈለግ ትጀምራለህ። ውጤቱ? ልትቆጣጠረው የማትችለው እንደሆነ ይሰማህ የነበረውን ሁኔታ በተወሰነ መጠንም ቢሆን መቆጣጠር ትጀምራለህ።—ኢዮብ 2:10

ይህን አስታውስ፦ አንድን ተራራ በአንድ እርምጃ ለመውጣት መሞከር የማይመስል ነገር ነው፤ ይሁን እንጂ ቀስ በቀስ እየተራመድክ አስቸጋሪውን ጉዞ መወጣት ትችላለህ። አብዛኞቹ የሚያጋጥሙህ ችግሮች ምንም ያህል እንደ ተራራ ገዝፈው ቢታዩህ በተመሳሳይ መንገድ ልትወጣቸው ትችላለህ።

ዛሬ ምን ማድረግ ትችላለህ? ሁኔታውን በተመለከተ ከአንድ ሰው ምናልባትም ከጓደኛህ ወይም ከቤተሰብህ አባል ጋር ተነጋገር። ይህ ሰው ያለህበትን ሁኔታ ይበልጥ ሚዛናዊ በሆነ መንገድ እንድታይ ሊረዳህ ይችል ይሆናል።—ምሳሌ 11:14

ሁኔታቸው ተለውጧል

መኖር እስኪያስጠላቸው ድረስ በሕይወታቸው የተመረሩ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ አራት ታማኝ ሰዎችን እንመልከት።

  • ርብቃ፦ “ዔሳው ባገባቸው በኬጢያውያን ሴቶች ምክንያት መኖር አስጠልቶኛል፤ ያዕቆብም ከዚሁ አገር ከኬጢያውያን ሴቶች ሚስት የሚያገባ ከሆነ፣ ሞቴን እመርጣለሁ።”—ዘፍጥረት 27:46

  • ሙሴ፦ “አሁኑኑ ግደለኝ፤ የሚደርስብኝን ጥፋት አልይ።”—ዘኍልቍ 11:15

  • ኤልያስ፦ “በቅቶኛል፤ እኔ ከቀደሙት አባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰዳት።”—1 ነገሥት 19:4

  • ኢዮብ፦ “ምነው ገና ስወለድ በጠፋሁ!”—ኢዮብ 3:11

የእነዚህን ሰዎች ታሪክ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስታነብ የነበሩበት ሁኔታ ባልጠበቁት መንገድ እንደተለወጠ ማየት ትችላለህ። የአንተም ሁኔታ ሊለወጥ ይችላል። (መክብብ 11:6) በመሆኑም ተስፋ አትቁረጥ!

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ