የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 13
  • የአምላክ ወዳጅ የሆነው አብርሃም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአምላክ ወዳጅ የሆነው አብርሃም
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አብርሃምና ሣራ አምላክን ታዘዋል
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • የአንባብያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • አብርሃም ማን ነበር?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • የአብርሃም ዓይነት እምነት አላችሁን?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1999
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 13

ምዕራፍ 13

የአምላክ ወዳጅ የሆነው አብርሃም

ሰዎች ከዚያ የጥፋት ውኃ በኋላ ኑሯቸውን ከመሠረቱባቸው ቦታዎች አንዱ ዑር ይባል ነበር። ይህ ቦታ ጥሩ ጥሩ ቤቶች ያሉበት የታወቀ ከተማ ሆኖ ነበር። ይሁን እንጂ በከተማው ውስጥ ይኖሩ የነበሩት ሰዎች የሐሰት አማልክትን ያመልኩ ነበር። በባቤልም ውስጥ ሳሉ ይህንኑ ያደርጉ ነበር። በዑርና በባቤል ውስጥ የነበሩ ሰዎች ይሖዋን ያገለግሉ እንደነበሩት እንደ ኖኅና እንደ ልጁ ሴም አልነበሩም።

በመጨረሻ፣ ያ የጥፋት ውኃ ከደረሰ ከ350 ዓመታት በኋላ ታማኙ ኖኅ ሞተ። በዚህ ሥዕል ላይ የምታየው ሰው የተወለደው ኖኅ ከሞተ ከሁለት ዓመታት በኋላ ነው። ከአምላክ ጋር ልዩ ዝምድና የነበረው ሰው ነበር። ይህ ሰው አብርሃም ይባላል። በዑር ከተማ ከቤተሰቡ ጋር ይኖር ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ይሖዋ አብርሃምን ‘ከዘመዶችህ ተለይተህ ዑርን ለቀህ ውጣ፤ እኔም ወደማሳይህ አገር ሂድ’ አለው። አብርሃም አምላክን በመታዘዝ በዑር የነበረውን ምቾት የተሞላበት ኑሮ ትቶ ወጥቷልን? አዎ፣ ወጥቷል። አብርሃም የአምላክ ወዳጅ ተብሎ ሊጠራ የቻለውም ሁልጊዜ አምላክን ይታዘዝ ስለነበረ ነው።

አብርሃም ዑርን ለቆ ሲወጣ ከቤተሰቡ መካከል አንዳንዶቹ አብረውት ሄደዋል። አባቱ ታራ አብሮት ሄዷል። የወንድሙ ልጅ ሎጥም አብሮት ሄዷል። የአብርሃም ሚስት የሆነችው ሣራም እንዲሁ አብራው ሄዳለች። ከጊዜ በኋላ ካራን ተብሎ ወደሚጠራው ቦታ ደረሱ፤ በዚያም ታራ ሞተ። ከዑር በጣም ርቀው ሄደው ነበር።

ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አብርሃምና ቤተሰቡ ካራንን ለቀቁና ከነዓን ተብሎ ወደሚጠራው ቦታ ሄዱ። እዚያም ከደረሱ በኋላ ይሖዋ ‘ለልጆችህ የምሰጣቸው ምድር ይህ ነው’ አለው። አብርሃምም በከነዓን ምድር በድንኳን ውስጥ ይኖር ጀመር።

አምላክ አብርሃምን ይረዳው ስለ ነበር የበጎቹና የእንስሳቱ መንጋ እየበዛ ሄደ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ አገልጋዮችም ነበሩት። ይሁን እንጂ እሱና ሣራ የራሳቸው ልጆች አልነበሯቸውም።

አብርሃም 99 ዓመት ሲሆነው ይሖዋ ‘የብዙ አሕዛብ አባት አደርግሃለሁ’ ብሎ ቃል ገባለት። ይሁን እንጂ አብርሃምና ሣራ በጣም አርጅተው ልጅ መውለድ በማይችሉበት ዕድሜ ላይ እያሉ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?

ዘፍጥረት 11:​27-32፤ 12:​1-7፤ 17:​1-8, 15-17፤ 18:​9-19

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ