የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 28
  • ሕፃኑ ሙሴ ከሞት የዳነበት ሁኔታ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሕፃኑ ሙሴ ከሞት የዳነበት ሁኔታ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሙሴ ይሖዋን ለማምለክ መረጠ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • “ለይሖዋ ዘምሩ”!
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
  • ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • ወላጆች ያሳዩት እምነት ወሮታ አስገኘ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1997
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 28

ምዕራፍ 28

ሕፃኑ ሙሴ ከሞት የዳነበት ሁኔታ

የሴትዮዋን ጣት ይዞ የሚያለቅሰውን ሕፃን ተመልከት። ይህ ሕፃን ሙሴ ነው። ይህች ቆንጆ ሴት ማን እንደሆነች ታውቃለህ? ግብፃዊት ልዕልት ናት፤ የራሱ የፈርዖን ልጅ ነች።

የሙሴ እናት ልጅዋ በግብፃውያን እንዲገደል ስላልፈለገች ሦስት ወር እስኪሞላው ድረስ ደብቃ አቆየችው። ይሁን እንጂ ሙሴን ሊያገኙት እንደሚችሉ ስላወቀች እርሱን ከሞት ለማዳን ስትል የሚከተለውን ነገር አደረገች።

በሣጥን መልክ የተዘጋጀ ቅርጫት ወሰደችና ውኃ እንዳያስገባ አድርጋ ሠራችው። ከዚያም ሙሴን እዚያ ውስጥ አስገባችውና በናይል ወንዝ አጠገብ ረጃጅም ሣር ባለበት ቦታ አስቀመጠችው። የሙሴ እህት ሚርያም በአቅራቢያው ቆማ የሚሆነውን ሁኔታ እንድትከታተል ታዝዛ ነበር።

ብዙም ሳይቆይ የፈርዖን ሴት ልጅ ልትታጠብ ወደ ናይል ወንዝ መጣች። ድንገት ይህን ቅርጫት በረጃጅም ሣር መካከል ተቀምጦ አየችው። ከአገልጋዮችዋ መካከል አንዷን ጠርታ ‘ሂጂና ያንን ቅርጫት አምጪልኝ’ አለቻት። ልዕልቷ ቅርጫቱን ስትከፍተው አንድ ቆንጆ ሕፃን አየች! ሕፃኑ ሙሴ እያለቀሰ ነበር፤ ልዕልቲቱ አዘነችለት። እንዲገደል አልፈለገችም።

ከዚያ በኋላ ሚርያም ወደ እነርሱ ተጠጋች። ሥዕሉ ላይ ልታያት ትችላለህ። ሚርያም የፈርዖንን ሴት ልጅ ‘ሕፃኑን የምታጠባልሽ እስራኤላዊት ሴት ልጥራልሽ?’ ብላ ጠየቀቻት።

ልዕልቲቱም ‘እባክሽ፣ ጥሪልኝ’ አለቻት።

ሚርያም ለእናቷ ለመንገር እየሮጠች ሄደች። የሙሴ እናት ወደ ልዕልቲቱ ስትመጣ ልዕልቲቱ ‘ይህን ሕፃን ውሰጂና አጥቢልኝ፤ ያሳደግሽበትን ዋጋ እከፍልሻለሁ’ አለቻት።

ስለዚህ የሙሴ እናት የራሷን ልጅ ማሳደግ ጀመረች። ከጊዜ በኋላ ሙሴ በደንብ ሲያድግ እናቱ ሙሴን የራስዋ ልጅ አድርጋ ለወሰደችው ለፈርዖን ልጅ ሰጠቻት። ሙሴ በፈርዖን ቤት ሊያድግ የቻለው በዚህ መንገድ ነበር።

ዘጸአት 2:​1-10

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ