የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 17 ገጽ 46-ገጽ 47 አን. 2
  • ሙሴ ይሖዋን ለማምለክ መረጠ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሙሴ ይሖዋን ለማምለክ መረጠ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • ሕፃኑ ሙሴ ከሞት የዳነበት ሁኔታ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ወላጆች ያሳዩት እምነት ወሮታ አስገኘ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1997
  • አንድ ክፉ ንጉሥ ግብፅን መግዛት ጀመረ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 17 ገጽ 46-ገጽ 47 አን. 2
የፈርዖን ልጅ ሕፃኑን ሙሴን ስታገኘው ሚርያም በአካባቢው ሆና እየተመለከተች ነው

ትምህርት 17

ሙሴ ይሖዋን ለማምለክ መረጠ

የያዕቆብ ቤተሰቦች ወደ ግብፅ ከሄዱ በኋላ እስራኤላውያን ተብለው መጠራት ጀመሩ። ያዕቆብና ዮሴፍ ከሞቱ በኋላ አዲስ ፈርዖን በግብፅ ላይ መግዛት ጀመረ። ይህ ንጉሥ እስራኤላውያን ከግብፃውያን የበለጠ ኃያል እንዳይሆኑ ፈርቶ ነበር። ስለሆነም ፈርዖን እስራኤላውያንን ባሪያዎች አደረጋቸው። ጡብ እንዲሠሩ እንዲሁም በእርሻ ቦታ ላይ እንደ ባሪያ እንዲያገለግሉ አደረገ። ግብፃውያን እንደ ባሪያ ቢያሠሯቸውም የእስራኤላውያን ቁጥር እየጨመረ ሄደ። ፈርዖን ይህ ሁኔታ ስላሳሰበው እስራኤላውያን የሚወልዷቸው ወንዶች ልጆች በሙሉ እንዲገደሉ አዘዘ። እስራኤላውያን ምን ያህል ፈርተው ሊሆን እንደሚችል ልትገምት ትችላለህ?

በዚህ ጊዜ ዮካቤድ የተባለች አንዲት እስራኤላዊት የሚያምር ወንድ ልጅ ወለደች። ልጁ እንዳይገደል ስትል ቅርጫት ውስጥ አድርጋ በአባይ ወንዝ ዳር በሚገኝ ቄጠማ መሃል ደበቀችው። የልጁ እህት የሆነችው ሚርያም በአካባቢው ሆና የሚሆነውን ነገር ትከታተል ነበር።

የፈርዖን ሴት ልጅ ወንዙ ውስጥ ገላዋን ልትታጠብ ስትመጣ ቅርጫቱን አየችው። ቅርጫቱ ውስጥ ያለው ሕፃን እያለቀሰ መሆኑን ስታይ አዘነችለት። ሚርያምም ‘ልጁን እያጠባች የምታሳድግልሽ ሞግዚት ልፈልግልሽ?’ ብላ ጠየቀቻት። የፈርዖን ልጅ በሐሳቡ ስትስማማ ሚርያም እናቷን ዮካቤድን ይዛ መጣች። የፈርዖን ልጅ ዮካቤድን ‘ልጁን ተንከባክበሽ አሳድጊልኝ፤ እኔ ገንዘብ እከፍልሻለሁ’ አለቻት።

ሙሴ ሲሸሽ

ልጁ ሲያድግ ዮካቤድ ወደ ፈርዖን ልጅ አመጣችው፤ የፈርዖን ልጅም ሙሴ ብላ ስም ያወጣችለት ሲሆን እንደ ራሷ ልጅ አድርጋ አሳደገችው። ሙሴ የንጉሥ ልጅ ሆኖ አደገ፤ በመሆኑም የፈለገውን ነገር ሁሉ ማግኘት ይችል ነበር። ሆኖም ሙሴ ይሖዋን አልረሳም። በፈርዖን ቤት ቢያድግም እስራኤላዊ እንጂ ግብፃዊ እንዳልሆነ ያውቅ ነበር። ስለዚህ ይሖዋን ለማገልገል መረጠ።

ሙሴ 40 ዓመት ሲሞላው እስራኤላውያንን ለመርዳት ወሰነ። አንድ ግብፃዊ አንድን እስራኤላዊ ባሪያ ሲደበድብ አየና ግብፃዊውን መትቶ ገደለው። ከዚያም አሸዋ ውስጥ ደበቀው። ፈርዖን ይህን ሲሰማ ሙሴን ለመግደል ሞከረ። ሆኖም ሙሴ ሸሽቶ ወደ ምድያም ምድር ሄደ። እዚያ ከሄደ በኋላ ይሖዋ ሙሴን ተንከባክቦታል።

‘ሙሴ የፈርዖን የልጅ ልጅ ተብሎ ለመጠራት በእምነት እንቢ አለ፤ ከአምላክ ሕዝብ ጋር መንገላታትን መረጠ።’—ዕብራውያን 11:24, 25

ጥያቄ፦ ግብፃውያን በእስራኤላውያን ላይ ምን በደል ይፈጽሙ ነበር? ሙሴ ወደ ምድያም የሸሸው ለምንድን ነው?

ዘፍጥረት 49:33፤ ዘፀአት 1:1-14, 22፤ 2:1-15፤ የሐዋርያት ሥራ 7:17-29፤ ዕብራውያን 11:23-27

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ