የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 49
  • ፀሐይ ባለችበት ቦታ ቆመች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ፀሐይ ባለችበት ቦታ ቆመች
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ኢያሱና ገባኦናውያን
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ኢያሱ 1:9—“ጽና፣ አይዞህ”
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችና ማብራሪያቸው
  • ኢያሱ ካሳለፈው ተሞክሮ ያገኘው ጥቅም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • እንዲሳካልን ይፈልጋል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 49

ምዕራፍ 49

ፀሐይ ባለችበት ቦታ ቆመች

ኢያሱን ተመልከተው። ‘ፀሐይ ትቁም!’ እያለ ነው። ፀሐይዋ ቆመች። በሰማይ መካከል አንድ ሙሉ ቀን ቆመች። ይሖዋ ፀሐይዋ እንድትቆም አደረገ! ይሁን እንጂ ኢያሱ ፀሐይ ብርሃንዋን መስጠትዋን እንድትቀጥል የፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ እስቲ እንመልከት።

በከነዓን ምድር የነበሩት አምስቱ መጥፎ ነገሥታት ገባዖናውያንን መውጋት ሲጀምሩ ገባዖናውያን ኢያሱ እንዲረዳቸው ለመጠየቅ ሰው ላኩ። መልእክተኛው ‘በፍጥነት ድረስልን! አድነን! በኮረብታማው አገር የሚኖሩ ነገሥታት በሙሉ አገልጋዮችህን ለመውጋት መጥተዋል’ አለው።

ወዲያውኑ ኢያሱና ተዋጊዎቹ በሙሉ ሄዱ። ሙሉ ሌሊት ተጓዙ። ገባዖን ሲደርሱ የአምስቱ ነገሥታት ወታደሮች ፈሩና መሸሽ ጀመሩ። ከዚያም ይሖዋ ትልልቅ የበረዶ ድንጋይ ከሰማይ አዘነበ፤ በበረዶው ድንጋይ ተመትተው የሞቱት ወታደሮች የኢያሱ ተዋጊዎች ከገደሏቸው ይበልጡ ነበር።

ኢያሱ ፀሐይ የምትጠልቅበት ጊዜ እየተቃረበ እንዳለ ተገንዝቦ ነበር። ቀኑ ይጨልምና ብዙዎቹ የአምስቱ መጥፎ ነገሥታት ወታደሮች ያመልጣሉ። ኢያሱ ወደ ይሖዋ በመጸለይ ‘ፀሐይ ትቁም!’ ያለው በዚህ ምክንያት ነበር። ፀሐይ ብርሃን መስጠቷን ስትቀጥል እስራኤላውያን ውጊያውን በአሸናፊነት ማጠናቀቅ ይችላሉ።

የአምላክን ሕዝብ የሚጠሉ ሌሎች ብዙ መጥፎ ነገሥታት በከነዓን ምድር ይገኙ ነበር። ኢያሱና ሠራዊቱ በዚያ ምድር ይኖሩ የነበሩትን 31 ነገሥታት ድል ለማድረግ ወደ ስድስት ዓመታት ገደማ ወስዶባቸዋል። ይህ ከሆነ በኋላ ኢያሱ የከነዓን ምድር ርስት ላላገኙት ነገዶች እንዲከፋፈል አደረገ።

ብዙ ዓመታት አለፉ፤ በመጨረሻም ኢያሱ በ110 ዓመቱ ሞተ። እሱና ጓደኞቹ በሕይወት በነበሩበት ዘመን ሁሉ ሕዝቡ ይሖዋን ይታዘዙ ነበር። እነዚህ ጥሩ ሰዎች ሲሞቱ ግን ሕዝቡ መጥፎ ነገሮች መሥራት ጀመሩና ችግር ውስጥ ገቡ። በዚህ ወቅት የአምላክን እርዳታ ማግኘት ያስፈልጋቸው ነበር።

ኢያሱ 10:​6-15፤ 12:​7-24፤ 14:​1-5፤ መሳፍንት 2:​8-13

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ