የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 31 ገጽ 78
  • ኢያሱና ገባኦናውያን

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢያሱና ገባኦናውያን
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ጥበበኞቹ ገባዖናውያን
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ፀሐይ ባለችበት ቦታ ቆመች
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ኢያሱ 1:9—“ጽና፣ አይዞህ”
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችና ማብራሪያቸው
  • ኢያሱ ካሳለፈው ተሞክሮ ያገኘው ጥቅም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 31 ገጽ 78
ገባኦናውያን ያረጀ ልብስ ለብሰው ወደ ኢያሱና ወደ ሠራዊቱ መጡ

ትምህርት 31

ኢያሱና ገባኦናውያን

በከነአን ምድር የሚገኙ ሌሎች ሕዝቦች በኢያሪኮ ላይ የደረሰውን ጥፋት ሰሙ። በመሆኑም የእነዚህ ሕዝቦች ነገሥታት ተባብረው ከእስራኤላውያን ጋር ለመዋጋት ወሰኑ። ገባኦናውያን ግን ሌላ ነገር ለማድረግ አሰቡ። ያረጀ ልብስ ለብሰው ወደ ኢያሱ ሄዱና እንዲህ አሉት፦ ‘የመጣነው ከሩቅ አገር ነው። ስለ ይሖዋም ሆነ በግብፅና በሞዓብ ምድር ለእናንተ ስላደረገው ነገር ሰምተናል። እባካችሁ ጥቃት እንደማትሰነዝሩብን ቃል ግቡልን፤ እኛም አገልጋዮቻችሁ እንሆናለን።’

ኢያሱ የተናገሩትን ነገር ስላመነ በእነሱ ላይ ጥቃት ላለመሰንዘር ተስማማ። ከሦስት ቀን በኋላ ግን ገባኦናውያን የሩቅ አገር ሰዎች ሳይሆኑ በዚያው በከነአን ምድር የሚኖሩ ሰዎች እንደሆኑ አወቀ። ኢያሱ ገባኦናውያንን ‘ለምንድን ነው ያታለላችሁን?’ በማለት ጠየቃቸው። እነሱም እንዲህ ብለው መለሱ፦ ‘ስለፈራን ነው! አምላካችሁ ይሖዋ ለእናንተ እንደሚዋጋላችሁ እናውቃለን። እባካችሁ አትግደሉን።’ ኢያሱም ቃሉን በመጠበቅ ሳይገድላቸው ቀረ።

ብዙም ሳይቆይ፣ በከነአን ምድር የሚኖሩ አምስት ነገሥታት ወታደሮቻቸውን አሰልፈው ከገባኦናውያን ጋር ለመዋጋት ተነሱ። ኢያሱና ሠራዊቱ ሌሊቱን ሙሉ ተጉዘው ገባኦናውያንን ለማዳን መጡ። በቀጣዩ ቀን ጠዋት ጦርነቱ ተጀመረ። ከነአናውያን በሁሉም አቅጣጫ መሸሽ ጀመሩ። በሸሹበት ቦታ ሁሉ ይሖዋ የበረዶ ድንጋይ አወረደባቸው። ከዚያም ኢያሱ ‘በገባኦን ላይ ፀሐይ ትቁም’ ብሎ ይሖዋን ለመነ። ፀሐይ ከዚያ በፊት ቆማ አታውቅም፤ ታዲያ ኢያሱ ፀሐይ እንድትቆም ይሖዋን የጠየቀው ለምንድን ነው? በይሖዋ ስለታመነ ነው። ፀሐይዋ እስራኤላውያን እነዚያን የከነአን ነገሥታትና ሠራዊታቸውን በሙሉ ድል አድርገው እስኪጨርሱ ድረስ አንድ ሙሉ ቀን ሳትጠልቅ ቆየች።

ኢያሱ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ፀሐይ እንድትቆም ይሖዋን ሲጠይቅ

“ቃላችሁ ‘አዎ’ ከሆነ አዎ ይሁን፤ ‘አይደለም’ ከሆነ አይደለም ይሁን፤ ከዚህ ውጭ የሆነ ግን ከክፉው ነው።”—ማቴዎስ 5:37

ጥያቄ፦ ገባኦናውያን ሕይወታቸውን ለማዳን ሲሉ ምን አደረጉ? ይሖዋ እስራኤላውያንን የረዳቸው እንዴት ነው?

ኢያሱ 9:1–10:15

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ