የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jl ትምህርት 13
  • አቅኚነት ምንድን ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አቅኚነት ምንድን ነው?
  • በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአቅኚነት አገልግሎት የሚያስገኛቸው በረከቶች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1997
  • አቅኚነት ከአምላክ ጋር ያለንን ዝምድና ያጠናክርልናል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • አቅኚዎች በረከትን ይሰጣሉ፤ መልሰውም በረከት ያገኛሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1994
  • አቅኚ መሆን ትችላለህን?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—1998
በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
jl ትምህርት 13

ትምህርት 13

አቅኚነት ምንድን ነው?

በአገልግሎት ላይ ያሉ የሙሉ ጊዜ ወንጌላውያን

ካናዳ

በስብከቱ ሥራ ላይ ያሉ የሙሉ ጊዜ ወንጌላውያን

ከቤት ወደ ቤት

አቅኚዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ሲመሩ

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

አንዲት አቅኚ መጽሐፍ ቅዱስን ስታጠና

የግል ጥናት

“አቅኚ” የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ የሚሠራበት ወደ አዲስ አካባቢ የሚሄዱ እንዲሁም ፈር ቀዳጅ በመሆን ለሌሎች መንገድ የሚጠርጉ ሰዎችን ለማመልከት ነው። ኢየሱስ፣ ሕይወት የሚያስገኝ አገልግሎት ለማከናወንና ወደ መዳን የሚመራውን በር ለመክፈት ወደ ምድር በመምጣቱ አቅኚ ሊባል ይችላል። (ማቴዎስ 20:28) በዛሬው ጊዜም ተከታዮቹ፣ ሰዎችን ‘ደቀ መዛሙርት በማድረጉ’ ሥራ የሚችሉትን ያህል ጊዜ በማሳለፍ የእሱን ምሳሌ እየተከተሉ ነው። (ማቴዎስ 28:19, 20) አንዳንድ የኢየሱስ ተከታዮች ደግሞ የአቅኚነት አገልግሎት ብለን በምንጠራው መስክ ይካፈላሉ።

አቅኚዎች የሙሉ ጊዜ ወንጌላውያን ናቸው። ሁሉም የይሖዋ ምሥክሮች የምሥራቹ አስፋፊዎች ወይም ሰባኪዎች ናቸው። አንዳንዶች ግን ፕሮግራማቸውን አስተካክለው በየወሩ 70 ሰዓት በስብከቱ ሥራ በማሳለፍ የዘወትር አቅኚዎች ሆነው ያገለግላሉ። ብዙዎች ይህን ለማድረግ ሲሉ በሰብዓዊ ሥራቸው ላይ የሚያሳልፉትን ጊዜ ይቀንሳሉ። ሌሎች ደግሞ የመንግሥቱ ሰባኪዎች ይበልጥ በሚያስፈልጉባቸው አካባቢዎች ልዩ አቅኚዎች ሆነው እንዲያገለግሉ የሚመደቡ ሲሆን እነዚህ ክርስቲያኖች በስብከቱ ሥራ በየወሩ 130 ሰዓት ወይም ከዚያ በላይ ያሳልፋሉ። አቅኚዎች ይሖዋ የሚያስፈልጓቸውን መሠረታዊ ነገሮች እንደሚያሟላላቸው ቅንጣት ታክል ስለማይጠራጠሩ ባላቸው በመርካት ቀለል ያለ ሕይወት ይመራሉ። (ማቴዎስ 6:31-33፤ 1 ጢሞቴዎስ 6:6-8) ልዩ ወይም የዘወትር አቅኚ መሆን የማይችሉ ክርስቲያኖች ደግሞ በሚመቻቸው ወር ረዳት አቅኚዎች ሆነው የሚያገለግሉ ሲሆን በዚያ ወቅት በስብከቱ ሥራ በወር ውስጥ 30 ወይም 50 ሰዓት ያሳልፋሉ።

አቅኚዎች በዚህ መስክ እንዲሰማሩ የሚያነሳሳቸው ለይሖዋና ለሰዎች ያላቸው ፍቅር ነው። ኢየሱስ በዘመኑ የነበሩት ሰዎች ያሉበትን መንፈሳዊ ሁኔታ ሲመለከት አዝኖላቸው ነበር፤ እኛም በዛሬው ጊዜ ብዙ ሰዎች ያሉበት መንፈሳዊ ሁኔታ አሳዛኝ እንደሆነ እናስተውላለን። (ማርቆስ 6:34) በሌላ በኩል ደግሞ ሰዎች ለወደፊቱ ጊዜ አስተማማኝ ተስፋ እንዲኖራቸው የሚያደርግ እውቀት እንዳለን እንገነዘባለን፤ ይህ እውቀት በአሁኑ ጊዜም እንኳ ሊጠቅማቸው ይችላል። አቅኚዎች ለሰዎች ያላቸው ፍቅር ሌሎችን በመንፈሳዊ ለመርዳት ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሳይቆጥቡ በስብከቱ ሥራ እንዲያሳልፉ ያነሳሳቸዋል። (ማቴዎስ 22:39፤ 1 ተሰሎንቄ 2:8) እንዲህ በማድረጋቸው እምነታቸው የሚጠናከርና ወደ አምላክ ይበልጥ የሚቀርቡ ከመሆኑም ሌላ ይህ ነው የማይባል ደስታ ያገኛሉ።—የሐዋርያት ሥራ 20:35

  • አቅኚነት ምንድን ነው?

  • አንዳንዶች በአቅኚነት እንዲካፈሉ የሚያነሳሳቸው ምንድን ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ