የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • T-34 ገጽ 1-4
  • መከራ የማይኖርበት ጊዜ ይመጣል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መከራ የማይኖርበት ጊዜ ይመጣል?
  • መከራ የማይኖርበት ጊዜ ይመጣል?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ስለ ወደፊቱ ጊዜ ምን ይሰማሃል?
    ስለ ወደፊቱ ጊዜ ምን ይሰማሃል?
  • የሞቱ ሰዎች እንደገና በሕይወት መኖር ይችላሉ?
    የሞቱ ሰዎች እንደገና በሕይወት መኖር ይችላሉ?
  • የአምላክ መንግሥት ምንድን ነው?
    የአምላክ መንግሥት ምንድን ነው?
  • ዓለምን እየተቆጣጠረ ያለው ማን ነው?
    ዓለምን እየተቆጣጠረ ያለው ማን ነው?
ለተጨማሪ መረጃ
መከራ የማይኖርበት ጊዜ ይመጣል?
T-34 ገጽ 1-4

መከራ የማይኖርበት ጊዜ ይመጣል?

መልስህ ምንድን ነው?

  • ይመጣል?

  • አይመጣም?

  • ወይስ ምናልባት?

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

“እሱም እንባን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሞት አይኖርም፤ ሐዘንም ሆነ ጩኸት እንዲሁም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይኖርም።” —ራእይ 21:3, 4 አዲስ ዓለም ትርጉም

ይህን ማወቅህ ለአንተ ምን ጥቅም አለው?

በሰው ልጆች ላይ ለሚደርሱት ችግሮች መንስኤው አምላክ እንዳልሆነ ማረጋገጫ ይሰጥሃል።—ያዕቆብ 1:13

መከራ ሲደርስብህ አምላክ እንደሚያዝንልህ ስለምታውቅ ትጽናናለህ።—ዘካርያስ 2:8

ሁሉም ዓይነት መከራ እንደሚወገድ ተስፋ እንድታደርግ ይረዳሃል።—መዝሙር 37:9-11

አንድ ሰው ከመከራና ከኢፍትሐዊነት የጸዳ ዓለምን በዓይነ ሕሊናው እየተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነብ

መጽሐፍ ቅዱስ በሚናገረው ነገር ላይ እምነት መጣል እንችላለን?

አዎ፣ ቢያንስ ሁለት ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል፦

  • አምላክ መከራንና ኢፍትሐዊነትን ይጠላል። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን፣ ይሖዋ አምላክ በሕዝቦቹ ላይ ግፍ ሲፈጸም ምን እንደተሰማው እስቲ እንመልከት። ሕዝቡ “በሚጨቁኗቸውና በሚያንገላቷቸው ሰዎች የተነሳ ሲቃትቱ” አምላክ እንዳዘነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።—መሳፍንት 2:18

    አምላክ በሌሎች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሰዎችን ይጠላል። ለምሳሌ ያህል፣ “ንጹሕ ደም የሚያፈሱ እጆች” በአምላክ ዘንድ የተጠሉ እንደሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።—ምሳሌ 6:16, 17

  • አምላክ በግለሰብ ደረጃ ያስብልናል። አንድ ሰው መከራ አጋጥሞት ‘ጭንቀትና ሥቃይ’ ሲሰማው ይሖዋም የዚህ ሰው ‘ጭንቀትና ሥቃይ’ ይሰማዋል።—2 ዜና መዋዕል 6:29, 30

    ይሖዋ በመንግሥቱ አማካኝነት የእያንዳንዱን ሰው መከራ በቅርቡ ያስወግዳል። (ማቴዎስ 6:9, 10) እስከዚያው ግን እሱን ከልብ የሚፈልጉ ሰዎችን በደግነት ያጽናናቸዋል።—የሐዋርያት ሥራ 17:27፤ 2 ቆሮንቶስ 1:3, 4

ምን ይመስልሃል?

ሁለት ሴቶች መጽሐፍ ቅዱስን እያጠኑ

አምላክ መከራ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ ሮም 5:12 እና 2 ጴጥሮስ 3:9 ላይ ይገኛል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ