መጠመቅ ለሚፈልጉ የቀረቡ ጥያቄዎች
ክፍል 1፦ የክርስትና ትምህርቶች
ከይሖዋ ምሥክሮች ጋር መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናትህ እውነትን እንድታውቅ አስችሎሃል። ያገኘኸው ትምህርት ከአምላክ ጋር ጥሩ ዝምድና እንዲኖርህ እንዲሁም በአምላክ መንግሥት አገዛዝ ሥር ገነት በምትሆነው ምድር ላይ የዘላለም ሕይወትና ሌሎች በረከቶች የመውረስ ተስፋ አስገኝቶልሃል። በአምላክ ቃል ላይ ያለህ እምነት ተጠናክሯል፤ እንዲሁም በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ በመታቀፍህ በአሁኑ ጊዜም እንኳ ብዙ በረከቶችን አግኝተሃል። ከዚህም ሌላ ይሖዋ በዛሬው ጊዜ ያሉ ሕዝቦቹን የሚይዝበትን መንገድ መገንዘብ ችለሃል።—ዘካ. 8:23
ለመጠመቅ እየተዘጋጀህ ስለሆነ ክርስቲያኖች ስለሚያምኑባቸው መሠረታዊ ትምህርቶች ከጉባኤ ሽማግሌዎች ጋር መወያየትህ ይጠቅምሃል። (ዕብ. 6:1-3) ይሖዋ እሱን ለማወቅ የምታደርገውን ጥረት ሁሉ ይባርክልህ፤ እንዲሁም ቃል የገባውን ሽልማት ለመውረስ ያብቃህ።—ዮሐ. 17:3
1. መጠመቅ የምትፈልገው ለምንድን ነው?
2. ይሖዋ ማን ነው?
• “በላይ በሰማይም ሆነ በታች በምድር እውነተኛው አምላክ፣ ይሖዋ እንደሆነ ዛሬ እወቅ፤ እንዲሁም ልብ በል። ሌላ ማንም የለም።”—ዘዳ. 4:39
• “ስምህ ይሖዋ የሆነው አንተ፣ አዎ፣ አንተ ብቻ በመላው ምድር ላይ ልዑል [ነህ]።”—መዝ. 83:18
3. አምላክን በግል ስሙ መጥራትህ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
• “እናንተ በዚህ መንገድ ጸልዩ፦ ‘በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ።’”—ማቴ. 6:9
• “የይሖዋን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል።”—ሮም 10:13
4. በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይሖዋን ለመግለጽ የተሠራባቸው አንዳንድ አገላለጾች የትኞቹ ናቸው?
• “የምድር ዳርቻዎች ፈጣሪ የሆነው ይሖዋ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላክ ነው።”—ኢሳ. 40:28
• “በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ።”—ማቴ. 6:9
• “አምላክ ፍቅር ነው።”—1 ዮሐ. 4:8
5. ለይሖዋ አምላክ ልትሰጠው የምትችለው ምንድን ነው?
• “አምላክህን ይሖዋን በሙሉ ልብህ፣ በሙሉ ነፍስህ፣ በሙሉ አእምሮህና በሙሉ ኃይልህ ውደድ።”—ማር. 12:30
• “ይሖዋ አምላክህን ብቻ አምልክ፤ ለእሱም ብቻ ቅዱስ አገልግሎት አቅርብ።”—ሉቃስ 4:8
6. ለይሖዋ ታማኝ መሆን የምትፈልገው ለምንድን ነው?
• “ልጄ ሆይ፣ ለሚነቅፈኝ መልስ መስጠት እችል ዘንድ ጥበበኛ ሁን፤ ልቤንም ደስ አሰኘው።”—ምሳሌ 27:11
7. የምትጸልየው ወደ ማን ነው? የምትጸልየውስ በማን ስም ነው?
• “እውነት እውነት እላችኋለሁ፣ አብን ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትጠይቁት ይሰጣችኋል።”—ዮሐ. 16:23
8. ስለ ምን ነገሮች ልትጸልይ ትችላለህ?
• “እናንተ በዚህ መንገድ ጸልዩ፦ ‘በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ። መንግሥትህ ይምጣ። ፈቃድህ በሰማይ እየተፈጸመ እንዳለ ሁሉ በምድርም ላይ ይፈጸም። የዕለቱን ምግባችንን ዛሬ ስጠን፤ የበደሉንን ይቅር እንዳልን በደላችንን ይቅር በለን። ከክፉው አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን።’”—ማቴ. 6:9-13
• “በእሱ ላይ ያለን ትምክህት ይህ ነው፤ የምንጠይቀው ነገር ምንም ይሁን ምን ከፈቃዱ ጋር በሚስማማ ሁኔታ እስከለመንን ድረስ ይሰማናል።”—1 ዮሐ. 5:14
9. ይሖዋ የአንድን ሰው ጸሎት እንዳይሰማ የሚያደርገው ምን ሊሆን ይችላል?
• “እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ይጮኻሉ፤ እሱ ግን አይመልስላቸውም። ክፉ ድርጊት በመፈጸማቸው፣ በዚያን ጊዜ ፊቱን ይሰውርባቸዋል።”—ሚክ. 3:4
• “የይሖዋ ዓይኖች ጻድቃንን ይመለከታሉና፤ ጆሮዎቹም ምልጃቸውን ይሰማሉ፤ የይሖዋ ፊት ግን ክፉ ነገሮችን በሚያደርጉ ላይ ነው።”—1 ጴጥ. 3:12
10. ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው?
• “ስምዖን ጴጥሮስም ‘አንተ ክርስቶስ፣ የሕያው አምላክ ልጅ ነህ’ ብሎ መለሰለት።”—ማቴ. 16:16
11. ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው ለምንድን ነው?
• “የሰው ልጅም የመጣው ለማገልገልና በብዙ ሰዎች ምትክ ሕይወቱን ቤዛ አድርጎ ለመስጠት እንጂ እንዲገለገል አይደለም።”—ማቴ. 20:28
• “[ኢየሱስ] ግን ‘ለሌሎች ከተሞችም የአምላክን መንግሥት ምሥራች ማወጅ አለብኝ፤ ምክንያቱም የተላክሁት ለዚህ ዓላማ ነው’ አላቸው።”—ሉቃስ 4:43
12. ለኢየሱስ መሥዋዕት ያለህን አድናቆት ማሳየት የምትችለው እንዴት ነው?
• “በሕይወት ያሉትም ከእንግዲህ ለራሳቸው ከመኖር ይልቅ ለእነሱ ለሞተውና ለተነሳው እንዲኖሩ እሱ ለሁሉም ሞቷል።”—2 ቆሮ. 5:15
13. ኢየሱስ ምን ሥልጣን አለው?
• “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል።”—ማቴ. 28:18
• “አምላክ የላቀ ቦታ በመስጠት ከፍ ከፍ አደረገው፤ እንዲሁም ከሌላ ከማንኛውም ስም በላይ የሆነ ስም በደግነት ሰጠው።”—ፊልጵ. 2:9
14. የይሖዋ ምሥክሮች የበላይ አካል በኢየሱስ የተሾመው “ታማኝና ልባም ባሪያ” እንደሆነ ታምናለህ?
• “በተገቢው ጊዜ ምግባቸውን እንዲሰጣቸው ጌታው በቤተሰቦቹ ላይ የሾመው ታማኝና ልባም ባሪያ በእርግጥ ማን ነው?”—ማቴ. 24:45
15. መንፈስ ቅዱስ የራሱ ማንነት ያለው አካል ነው?
• “መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ ‘መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑሉም ኃይል በአንቺ ላይ ያርፋል። ስለሆነም የሚወለደው ልጅ ቅዱስና የአምላክ ልጅ ይባላል።’”—ሉቃስ 1:35
• “ታዲያ እናንተ ክፉዎች ሆናችሁ ሳለ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ በሰማይ ያለው አባትማ ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን እንዴት አብልጦ አይሰጣቸው!”—ሉቃስ 11:13
16. ይሖዋ ቅዱስ መንፈሱን የተጠቀመበት እንዴት ነው?
• “ሰማያት በይሖዋ ቃል፣ በውስጣቸው ያሉትም ሁሉ ከአፉ በሚወጣው መንፈስ ተሠሩ።”—መዝ. 33:6
• “መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በሚወርድበት ጊዜ ኃይል ትቀበላላችሁ፤ . . . እንዲሁም እስከ ምድር ዳር ድረስ ምሥክሮቼ ትሆናላችሁ።”—ሥራ 1:8
• “በቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ያለው ትንቢት ሁሉ በሰው ሐሳብ ላይ የተመሠረተ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ። መቼም ቢሆን ትንቢት በሰው ፈቃድ አልመጣምና፤ ከዚህ ይልቅ ሰዎች ከአምላክ የተቀበሉትን ትንቢት በመንፈስ ቅዱስ ተገፋፍተው ተናገሩ።”—2 ጴጥ. 1:20, 21
17. የአምላክ መንግሥት ምንድን ነው?
• “የሰማይ አምላክ ፈጽሞ የማይጠፋ መንግሥት ያቋቁማል። ይህም መንግሥት ለሌላ ሕዝብ አይሰጥም። እነዚህን መንግሥታት ሁሉ ያደቅቃል፤ ፈጽሞም ያጠፋቸዋል፤ እሱም ብቻውን ለዘላለም ይቆማል።”—ዳን. 2:44
18. የአምላክ መንግሥት ምን በረከት ያስገኝልሃል?
• “እንባን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሞት አይኖርም፤ ሐዘንም ሆነ ጩኸት እንዲሁም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይኖርም። ቀድሞ የነበሩት ነገሮች አልፈዋል።”—ራእይ 21:4
19. የአምላክ መንግሥት የሚያመጣቸው በረከቶች በቅርቡ እውን እንደሚሆኑ እንድታምን ያደረገህ ምንድን ነው?
• “ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እሱ መጥተው ‘እስቲ ንገረን፣ እነዚህ ነገሮች የሚፈጸሙት መቼ ነው? የመገኘትህና የዚህ ሥርዓት መደምደሚያ ምልክትስ ምንድን ነው?’ አሉት። ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦ ‘. . . ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሳልና፤ በተለያየ ስፍራ የምግብ እጥረትና የምድር ነውጥ ይከሰታል። ይህ የመንግሥቱ ምሥራች ለብሔራት ሁሉ ምሥክር እንዲሆን በመላው ምድር ይሰበካል፤ ከዚያም መጨረሻው ይመጣል።’”—ማቴ. 24:3, 4, 7, 14
• “በመጨረሻዎቹ ቀናት ለመቋቋም የሚያስቸግር በዓይነቱ ልዩ የሆነ ዘመን እንደሚመጣ ይህን እወቅ። ምክንያቱም ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ፣ ገንዘብ የሚወዱ፣ ጉረኞች፣ ትዕቢተኞች፣ ተሳዳቢዎች፣ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፣ የማያመሰግኑ፣ ታማኝ ያልሆኑ፣ ተፈጥሯዊ ፍቅር የሌላቸው፣ ለመስማማት ፈቃደኞች ያልሆኑ፣ ስም አጥፊዎች፣ ራሳቸውን የማይገዙ፣ ጨካኞች፣ ጥሩ ነገር የማይወዱ፣ ከዳተኞች፣ ግትሮች፣ በኩራት የተወጠሩ፣ ከአምላክ ይልቅ ሥጋዊ ደስታን የሚወዱ ይሆናሉ፤ ለአምላክ ያደሩ መስለው ይታያሉ፤ በሥራቸው ግን ኃይሉን ይክዳሉ።”—2 ጢሞ. 3:1-5
20. በሕይወትህ ውስጥ ለአምላክ መንግሥት ትልቅ ቦታ እንደምትሰጥ ማሳየት የምትችለው እንዴት ነው?
• “ከሁሉ አስቀድማችሁ የአምላክን መንግሥትና ጽድቅ ፈልጉ።”—ማቴ. 6:33
• “ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፦ ‘ሊከተለኝ የሚፈልግ ማንም ቢኖር ራሱን ይካድ፤ የራሱን የመከራ እንጨት ይሸከም፤ ያለማቋረጥም ይከተለኝ።’”—ማቴ. 16:24
21. ሰይጣን ማን ነው? አጋንንትስ እነማን ናቸው?
• “እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ፤ . . . እሱ በራሱ መንገድ መሄድ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ነፍሰ ገዳይ ነበር።”—ዮሐ. 8:44
• “ታላቁ ዘንዶ ይኸውም መላውን ዓለም እያሳሳተ ያለው ዲያብሎስና ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው የጥንቱ እባብ ወደ ታች ተወረወረ፤ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእሱ ጋር ተወረወሩ።”—ራእይ 12:9
22. ሰይጣን በይሖዋና ይሖዋን በሚያመልኩ ሰዎች ላይ ምን ክስ ሰንዝሯል?
• “ሴቲቱ እባቡን እንዲህ አለችው፦ ‘በአትክልቱ ስፍራ ካሉት ዛፎች ፍሬ መብላት እንችላለን። ይሁንና በአትክልቱ ስፍራ መካከል የሚገኘውን ዛፍ ፍሬ በተመለከተ አምላክ “ከእሱ አትብሉ፤ ፈጽሞም አትንኩት፤ አለዚያ ትሞታላችሁ” ብሏል።’ በዚህ ጊዜ እባቡ ሴቲቱን እንዲህ አላት፦ ‘መሞት እንኳ ፈጽሞ አትሞቱም። አምላክ ከዛፉ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንደሚገለጡና መልካምና ክፉን በማወቅ ረገድ እንደ አምላክ እንደምትሆኑ ስለሚያውቅ ነው።’”—ዘፍ. 3:2-5
• “ሰይጣን እንዲህ ሲል ለይሖዋ መለሰ፦ ‘ቁርበት ስለ ቁርበት ነው። ሰውም ለሕይወቱ ሲል ያለውን ነገር ሁሉ ይሰጣል።’”—ኢዮብ 2:4
23. ሰይጣን የሚሰነዝረው ክስ ሐሰት መሆኑን ማሳየት የምትችለው እንዴት ነው?
• “በሙሉ ልብ [አምላክን] አገልግለው።”—1 ዜና 28:9
• “እስክሞት ድረስ ንጹሕ አቋሜን አላጎድፍም!”—ኢዮብ 27:5
24. ሰዎች የሚሞቱት ለምንድን ነው?
• “በአንድ ሰው አማካኝነት ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ፤ በኃጢአትም ምክንያት ሞት መጣ፤ ሁሉም ኃጢአት ስለሠሩም ሞት ለሰው ሁሉ ተዳረሰ።”—ሮም 5:12
25. የሞቱ ሰዎች በምን ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ?
• “ሕያዋን እንደሚሞቱ ያውቃሉና፤ ሙታን ግን ምንም አያውቁም።”—መክ. 9:5
26. የሞቱ ሰዎች ምን ተስፋ አላቸው?
• “ጻድቃንም ሆኑ ዓመፀኞች ከሞት [ይነሳሉ]።”—ሥራ 24:15
27. ወደ ሰማይ ሄደው ከኢየሱስ ጋር የሚገዙት ሰዎች ምን ያህል ናቸው?
• “እነሆ፣ በጉ በጽዮን ተራራ ላይ ቆሟል፤ ከእሱም ጋር የእሱ ስምና የአባቱ ስም በግንባራቸው ላይ የተጻፈባቸው 144,000 ነበሩ።”—ራእይ 14:1