የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 11 ገጽ 32-ገጽ 33 አን. 2
  • የአብርሃም እምነት ተፈተነ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአብርሃም እምነት ተፈተነ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አምላክ የአብርሃምን እምነት ፈተነው
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ከሁሉ የላቀው የአምላክ ፍቅር ማረጋገጫ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ይሖዋ “ወዳጄ” በማለት ጠርቶታል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • አብርሃም ማን ነበር?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 11 ገጽ 32-ገጽ 33 አን. 2
አብርሃምና ይስሐቅ ወደ ሞሪያ ሲጓዙ

ትምህርት 11

የአብርሃም እምነት ተፈተነ

አብርሃም፣ ልጁ ይስሐቅ ይሖዋን እንዲወድና እሱ በገባው ቃል ላይ እምነት እንዲኖረው አስተምሮታል። ሆኖም ይስሐቅ 25 ዓመት አካባቢ ሲሆነው ይሖዋ አብርሃምን አንድ በጣም ከባድ ነገር እንዲያደርግ ጠየቀው። ይሖዋ ለአብርሃም ያቀረበው ጥያቄ ምን ነበር?

አምላክ አብርሃምን ‘እባክህ አንድ ልጅህን ወስደህ በሞሪያ ምድር በሚገኝ ተራራ ላይ መሥዋዕት አድርገህ አቅርበው’ አለው። አብርሃም፣ ይሖዋ እንዲህ እንዲያደርግ የጠየቀው ለምን እንደሆነ አላወቀም ነበር። ቢሆንም ይሖዋን ታዟል።

በማግስቱ ጠዋት አብርሃም ይስሐቅንና ሁለት አገልጋዮቹን ይዞ ወደ ሞሪያ ሄደ። ለሦስት ቀን ከተጓዙ በኋላ ከርቀት ተራራው ታያቸው። አብርሃም፣ እሱና ይስሐቅ መሥዋዕት አቅርበው እስኪመለሱ ድረስ አገልጋዮቹ እዚያው እንዲቆዩ ነገራቸው። አብርሃም ለእሳት ማንደጃ የሚሆነውን እንጨት ይስሐቅ እንዲሸከም አደረገ፤ እሱ ደግሞ ቢላውን ያዘ። ይስሐቅ አባቱን ‘መሥዋዕት የምናደርገው በግ የት አለ?’ ብሎ ጠየቀው። አብርሃምም ‘ልጄ፣ በጉን ይሖዋ ያዘጋጃል’ ብሎ መለሰለት።

በመጨረሻም ተራራው ጋ ሲደርሱ መሠዊያ ሠሩ። ከዚያም አብርሃም የይስሐቅን እጆችና እግሮች አስሮ መሠዊያው ላይ አስተኛው።

ይስሐቅ ታስሮ መሠዊያው ላይ ተኝቷል፤ አብርሃም ደግሞ በእጁ ቢላ ይዟል

አብርሃም ቢላውን አነሳ። በዚህ ጊዜ የይሖዋ መልአክ ከሰማይ እንዲህ አለው፦ ‘አብርሃም፣ ልጁን እንዳትነካው! ልጅህን እንኳ መሥዋዕት ለማድረግ ፈቃደኛ ስለሆንክ በአምላክ ላይ እምነት እንዳለህ አሁን አወቅኩ።’ ከዚያም አብርሃም አንድ አውራ በግ ቀንዶቹ በዛፍ ቅርንጫፎች ተይዘው አየ። ወዲያውኑ ይስሐቅን ፈታውና በጉን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።.

ከዚያ ቀን አንስቶ ይሖዋ አብርሃምን ‘ወዳጄ’ በማለት ይጠራው ጀመር። ለምን እንደሆነ ታውቃለህ? አብርሃም፣ ይሖዋ አንድ ነገር እንዲያደርግ ያዘዘው ለምን እንደሆነ ቢገባውም ባይገባውም ምንጊዜም ይታዘዝ ነበር።

አብርሃም ይስሐቅን ሲፈታው

ከዚያም ይሖዋ ለአብርሃም ‘እባርክሃለሁ፤ ዘርህን ወይም ልጆችህን አበዛልሃለሁ’ በማለት በድጋሚ ቃል ገባለት። በተጨማሪም ይሖዋ ጥሩ ሰዎችን በሙሉ በአብርሃም ቤተሰብ በኩል እንደሚባርክ ቃል ገባ።

“አምላክ ዓለምን እጅግ ከመውደዱ የተነሳ በልጁ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ ሲል አንድያ ልጁን ሰጥቷል።”—ዮሐንስ 3:16

ጥያቄ፦ አብርሃም በይሖዋ ላይ እምነት እንዳለው ያሳየው እንዴት ነው? ይሖዋ ለአብርሃም ምን ቃል ገባለት?

ዘፍጥረት 22:1-18፤ ዕብራውያን 11:17-19፤ ያዕቆብ 2:21-23

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ