የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 23 ገጽ 60-ገጽ 61 አን. 4
  • እስራኤላውያን ለይሖዋ ቃል ገቡ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እስራኤላውያን ለይሖዋ ቃል ገቡ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ ሕጎቹን ሰጠ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ሲና​—የሙሴና የምሕረት ተራራ
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • የይሖዋን መንገድ መማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • ቃላቸውን አልጠበቁም
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 23 ገጽ 60-ገጽ 61 አን. 4
እስራኤላውያን በሲና ተራራ ሥር ቆመው

ትምህርት 23

እስራኤላውያን ለይሖዋ ቃል ገቡ

እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ ከሁለት ወራት ገደማ በኋላ ወደ ሲና ተራራ ደረሱ፤ በዚያም ድንኳናቸውን ተከሉ። ሙሴ ወደ ተራራው ከወጣ በኋላ ይሖዋ ጠራውና እንዲህ አለው፦ ‘እስራኤላውያንን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ። ከታዘዙኝና ሕጎቼን ከጠበቁ ለእኔ ልዩ ሕዝብ ይሆናሉ።’ ከዚያም ሙሴ ተመልሶ ወረደና ይሖዋ ያለውን ነገር ለእስራኤላውያን ነገራቸው። እነሱም ‘ይሖዋ አድርጉ ያለንን ነገር በሙሉ እናደርጋለን’ ሲሉ መለሱ።

ሙሴ ተመልሶ ወደ ተራራው ወጣ። ይሖዋም እንዲህ አለው፦ ‘በሦስት ቀን ውስጥ አነጋግርሃለሁ። ሕዝቡ ወደ ሲና ተራራ ለመውጣት እንዳይሞክሩ አስጠንቅቃቸው።’ ሙሴ ከተራራው ወረደና እስራኤላውያንን ‘የይሖዋን ቃል ለመስማት ተዘጋጁ’ አላቸው።

እስራኤላውያን በሲና ተራራ ላይ የወረደውን መብረቅና ጥቁር ደመና ሲያዩ

በሦስተኛው ቀን፣ እስራኤላውያን ተራራው ላይ መብረቅና ጥቁር ደመና አዩ። የነጎድጓድና የቀንደ መለከት ድምፅም ሰሙ። ከዚያም ይሖዋ ወደ ተራራው በእሳት ወረደ። እስራኤላውያን በጣም ከመፍራታቸው የተነሳ ተንቀጠቀጡ። መላው ተራራ በኃይል ተናወጠ፤ እንዲሁም በጭስ ተሞላ። የቀንደ መለከቱ ድምፅም ይበልጥ እየጨመረ መጣ። ከዚያም አምላክ እንዲህ አለ፦ ‘እኔ ይሖዋ ነኝ። ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የለባችሁም።’

ሙሴ ተመልሶ ወደ ተራራው ወጣ፤ ይሖዋም ሕዝቡ እንዴት ሊያመልኩት እንደሚገባ እንዲሁም ማድረግ ያለባቸውንና የሌለባቸውን ነገሮች የሚገልጽ ሕግ ሰጠው። ሙሴ ሕጉን ጻፈና ለእስራኤላውያን አነበበላቸው። እነሱም ‘ይሖዋ እንድናደርግ ያዘዘንን ነገር በሙሉ እናደርጋለን’ በማለት ለአምላክ ቃል ገቡ። ታዲያ ቃላቸውን ይጠብቁ ይሆን?

“አምላክህን ይሖዋን በሙሉ ልብህ፣ በሙሉ ነፍስህና በሙሉ አእምሮህ ውደድ።”—ማቴዎስ 22:37

ጥያቄ፦ በሲና ተራራ ላይ ምን ተከናወነ? እስራኤላውያን ምን ለማድረግ ቃል ገቡ?

ዘፀአት 19:1–20:21፤ 24:1-8፤ ዘዳግም 7:6-9፤ ነህምያ 9:13, 14

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ