የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 36 ገጽ 88-ገጽ 89 አን. 1
  • ዮፍታሔ የገባው ቃል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዮፍታሔ የገባው ቃል
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ዮፍታሔ የገባው ቃል
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • አባቷንና ይሖዋን አስደስታለች
    ልጆቻችሁን አስተምሩ
  • በአምላክም ሆነ በጓደኞቿ ዘንድ ተወዳጅ ነበረች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • በይሖዋ ላይ እምነት ማሳደር የእሱን ሞገስ ያስገኛል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 36 ገጽ 88-ገጽ 89 አን. 1
ዮፍታሔ ልጁ ልትቀበለው መውጣቷን አይቶ ልብሱን ሲቀድ

ትምህርት 36

ዮፍታሔ የገባው ቃል

እስራኤላውያን በድጋሚ ይሖዋን ትተው የሐሰት አማልክትን ማምለክ ጀመሩ። አሞናውያን ጥቃት ሰንዝረውባቸው ከእነሱ ጋር በተዋጉበት ወቅት እነዚህ የሐሰት አማልክት ምንም አልረዷቸውም። እስራኤላውያን ለብዙ ዓመታት ሥቃይ ደረሰባቸው። በመጨረሻም ይሖዋን ‘ኃጢአት ሠርተናል። እባክህ ከጠላቶቻችን አድነን’ ብለው ለመኑት። እስራኤላውያን ጣዖቶቻቸውን አስወግደው ይሖዋን ማምለክ ጀመሩ። ይሖዋም ሲሠቃዩ ማየት አልፈለገም።

በመሆኑም ዮፍታሔ የተባለ አንድ ተዋጊ ሕዝቡን እየመራ ከአሞናውያን ጋር እንዲዋጋ ተመረጠ። ዮፍታሔ ለይሖዋ እንዲህ በማለት ቃል ገባ፦ ‘ይህን ጦርነት እንድናሸንፍ ከረዳኸን፣ ወደ ቤት ስመለስ ሊቀበለኝ የሚወጣውን የመጀመሪያ ሰው ለአንተ እሰጥሃለሁ።’ ይሖዋም የዮፍታሔን ጸሎት ሰምቶ በጦርነቱ እንዲያሸንፍ ረዳው።

ዮፍታሔ ወደ ቤቱ ሲመለስ በመጀመሪያ ልትቀበለው የወጣችው ልጁ ነበረች፤ ዮፍታሔ ከእሷ ሌላ ልጅ አልነበረውም። እየጨፈረችና ከበሮ እየመታች ልትቀበለው ወጣች። ዮፍታሔ ምን ያደርግ ይሆን? ለይሖዋ የገባውን ቃል አስታወሰና እንዲህ አለ፦ ‘ወይኔ፣ ልጄ! ልቤን ሰበርሽው። ለይሖዋ ቃል ገብቻለሁ። የገባሁትን ቃል ለመጠበቅ ደግሞ በሴሎ ባለው የማደሪያ ድንኳን እንድታገለግዪ አንቺን መላክ አለብኝ።’ በዚህ ጊዜ ልጁ እንዲህ አለችው፦ ‘አባዬ፣ ለይሖዋ ቃል ከገባህ ቃልህን መጠበቅ አለብህ። ብቻ ወደ ተራሮች ሄጄ ከሴት ጓደኞቼ ጋር ለሁለት ወር ያህል አብሬ ጊዜ እንዳሳልፍ ፍቀድልኝ። ከዚያ እሄዳለሁ።’ ከዚያ በኋላ የዮፍታሔ ልጅ ዕድሜዋን በሙሉ በማደሪያ ድንኳኑ በታማኝነት አገልግላለች። ጓደኞቿም በየዓመቱ ወደ ሴሎ እየሄዱ ይጠይቋት ነበር።

የዮፍታሔ ልጅ ጓደኞች እሷን ለመጠየቅ ወደ ማደሪያ ድንኳኑ ሄደው

“ከእኔ ይልቅ ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ሁሉ ለእኔ ሊሆን አይገባም።”—ማቴዎስ 10:37

ጥያቄ፦ ዮፍታሔ ለይሖዋ የገባው ቃል ምን ነበር? የዮፍታሔ ልጅ አባቷ የገባውን ቃል ስትሰማ ምን አደረገች?

መሳፍንት 10:6–11:11፤ 11:29-40፤ 1 ሳሙኤል 12:10, 11

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ