የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w93 8/1 ገጽ 9
  • የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎች ሪፖርት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎች ሪፖርት
  • መጠበቂያ ግንብ—1993
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ከባሕር እስከ ባሕር የተዘረጋ “የብረት መቀነት”
    ንቁ!—2010
  • ከኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያነት መንፈሳዊ ብርሃን ወደማንጸባረቅ ተለወጠ
    ንቁ!—2007
  • የይሖዋ ምስክሮች—ከስሙ በስተጀርባ ያለው ድርጅት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1992
  • ምሥክርነት ለመስጠት የሚረዱት የቪዲዮ ፊልሞች በሰዎች ላይ እያሳደሩ ያሉት በጎ ተጽዕኖ
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
ለተጨማሪ መረጃ
መጠበቂያ ግንብ—1993
w93 8/1 ገጽ 9

የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎች ሪፖርት

የባቡር ጉዞን እጅግ የሚያፈቅር አንድ ወጣት እውነትን አወቀ

አንድ ሰው ልቡ ወደ ጽድቅ ካዘነበለ ይሖዋ አምላክ ክርስቶስ ኢየሱስንና ሰማያዊ መላዕክቶቹን በመጠቀም እንዲህ ዓይነቱ በግ መሰል ሰው ውሎ አድሮ የመንግሥቱን ምሥራች እንዲያገኝ እንደሚያደርግ አያጠራጥርም። ከጊዜ በኋላ ይህ ሰው የኢየሱስን ሞገስ አግኝቶ በቀኙ ሊቆም ሊመጣ ይችላል። (ማቴዎስ 25:​31–33) ይህ ሁኔታ በኦስትሪያ በሚገኝ ለየት ባለ መንገድ እውነትን ባወቀ የባቡር ጉዞን እጅግ በሚያፈቀር አንድ ወጣት ላይ ተፈጽሟል።

ይህ ወጣት እጅግ የሚደሰትበት የጊዜ ማሳለፊያው በባቡር ጣቢያው አስተዳደር ፈቃድ ከባቡር ነጂው ጎን ተቀምጦ መጓዝ ነበር። ወደ ቤቱ ሲመለስ እንደገና ማየት እንዲችል እያንዳንዱን ጉዞ በቪዲዮ ካሜራው ይቀርጸው ነበር። ከቪየና ወደ ሳልስበርግ በሄደበት ወቅት የባቡር ነጂው ከይሖዋ ምስክሮች አንዱ ነበር። የባቡር ጉዞን እጅግ ለሚያፈቅረው ለዚህ ወጣት ስለ መንግሥቱ ለማነጋገር አጋጣሚውን ተጠቀመበት። በመጀመሪያ የባቡር ነጂው ስለ አምላክና ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መናገሩ ወጣቱን አስገርሞት ነበር፤ በጉዞው ወቅት ግን የባቡር ነጂው በሚነግረው ነገር ላይ ሳይሆን በሚያየው ነገር ላይ ይበልጥ አተኮረ።

ወደ ቤት ሲመለስ የባቡር ጉዞን እጅግ የሚያፈቅረው ይህ ወጣት በዚህ ጉዞ በጣም ተደስቶ ስለነበር የቪዲዮ ቅጂውን አንዴ ሳይሆን አሥር ጊዜ ተመለከተው። ድምፁንም ቀድቶት ስለነበር ምስክሩ የነገረውን ነገር ደጋግሞ ሰማው። ቪዲዮውን ደጋግሞ ባየ ቁጥር ከተነገረው ነገር ጋር በደንብ ተዋወቀ። ነገሩን አሰበበት፤ በመጨረሻም ከመጽሐፍ ቅዱስ ለቀረበው ግሩም የሆነ ትምህርት ጉጉት አደረበት። የበለጠ ለማወቅ ፈለገ።

የባቡር ነጂውን ስም አስታወሰ፤ በቪየና ውስጥ በሆነ ቦታ እንደሚኖርም ያውቅ ነበር። ስለዚህ ወደ ፖስታ ቤት ሄደና በስልክ ማውጫው ላይ በዚያ ስም የሰፈሩትን የስልክ ቁጥሮች አንድ በአንድ መደወል ጀመረ። ስልኩን ለሚያነሱት ሰዎች “የባቡር ነጂ ነዎትን?” የሚል ጥያቄ ያቀርብላቸው ነበር። አይደለሁም የሚል መልስ ከሰጡት ሌላውን ቁጥር ይደውል ነበር። በመጨረሻ የባቡር ነጂውን አገኘው። የሆነውን ነገር ተረከለትና በቪድዮው የሰማውን የመጽሐፍ ቅዱስ መልዕክት እንደተደሰተበት ገለጸለት።

ምስክሩ ወጣቱ በሚኖርበት አካባቢ የሚኖር አንድ ሰው እንዲያነጋግረው በቅርንጫፍ ቢሮ በኩል ሁኔታዎችን አመቻቸ። እንደ አጋጣሚ ሆኖ በዚያ አካባቢ በሚገኘው ጉባኤ የባቡር ነጂ የሆነ ሌላ ምስክር ይገኝ ነበር። ይህ ሁለተኛው የባቡር ነጂ የባቡር ጉዞን እጅግ የሚያፈቅረውን ወጣት አነጋገረውና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ተጀመረ። በ1991 የበጋ ወራት ወጣቱ ተጠመቀ።

ልብን ሁሉ የሚመረምረው ይሖዋ ይህ ሰው ለጽድቅ ልባዊ የሆነ ፍቅር እንዳለው አይቶ መሆን አለበት። ስለዚህም ለየት ባለ መንገድ ቢሆንም እንኳን የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት እንዲያገኝ አስችሎታል። — 1 ዜና መዋዕል 28:​9፤ ዮሐንስ 10:​27

[በገጽ 9 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

Courtesy of the Austrian Railways

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ