የአስተዳደር አካል ጭማሪ
የይሖዋ ምሥክሮች የአስተዳደር አካል ሠራተኞችን ብዛት ለመጨመር ሲባል በአሁኑ ጊዜ እያገለገሉ ባሉት 11 ሽማግሌዎች ላይ ከሐምሌ 1, 1994 ጀምሮ አንድ አባል ተጨምሯል። አዲሱ አባል ገሪት ሎይሽ ነው።
ወንድም ሎይሽ የሙሉ ጊዜ አገልግሎቱን የጀመረው ኅዳር 1, 1961 ሲሆን ከጊልያድ የመጠበቂያ ግንብ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት 41ኛ ክፍል የተመረቀ ነው። ከ1963 እስከ 1976 ድረስ በኦስትሪያ ውስጥ በክልልና በወረዳ የበላይ ተመልካችነት ሥራ አገልግሏል። በ1967 ካገባ በኋላ እሱና ባለቤቱ መሪት ቪየና በሚገኘው የኦስትሪያ ቅርንጫፍ ቢሮ የቤቴል ቤተሰብ አባላት ሆነው ለ14 ዓመታት አገልግለዋል። ከአራት ዓመታት በፊት በብሩክሊን ኒው ዮርክ ወደሚገኘው የማኅበሩ ዋና መሥሪያ ቤት ከተዛወሩ በኋላ ወንድም ሎይሽ በአስተዳደር ቢሮ ውስጥ እንዲሁም የአገልግሎት ኮሚቴ ረዳት በመሆን ሲያገለግል ነበር። በአውሮፓ መስክ ብዙ ተሞክሮ ያካበተና ጀርመንኛ፣ እንግሊዝኛ፣ የሩማኒያ ቋንቋና ጣሊያንኛ የሚያውቅ በመሆኑ ለአስተዳደር አካሉ ሥራ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል።