የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w15 1/1 ገጽ 3
  • መርዝ የሆነው ሙስና

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መርዝ የሆነው ሙስና
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሙስና መፍትሔ ይኖረው ይሆን?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • የአምላክ መንግሥት—ከሙስና የጸዳ መስተዳድር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ምግባረ ብልሹነት የሌለበት ዓለም እንደሚመጣ የተሰጠ ተስፋ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
  • ሙስና ምን ያህል ተስፋፍቷል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
w15 1/1 ገጽ 3
ሙሰኛ የሆነ አንድ ፖሊስ ጉቦ ሲቀበል

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | ከሙስና የጸዳ መንግሥት

መርዝ የሆነው ሙስና

በመንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ባለሥልጣናት ከሕዝብ ያገኙትን ሥልጣን ለግል ጥቅማቸው ሲያውሉት ይታያል። እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት በጥንት ዘመንም ነበር። ለምሳሌ ያህል፣ መጽሐፍ ቅዱስ ፍርድ ነክ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ሰዎች ጉቦ መቀበል እንደሌለባቸው የሚገልጽ ሕግ ይዟል፤ ይህ፣ እንዲህ ዓይነቱ ተግባር ከ3,500 ዓመታት በፊትም ይፈጸም እንደነበር ይጠቁማል። (ዘፀአት 23:8) እርግጥ ነው፣ ሙስና ሲባል ጉቦ መቀበል ማለት ብቻ አይደለም። ሙሰኛ የሆኑ የሕዝብ ባለሥልጣናት የሌሎችን ንብረት ይወርሳሉ፤ አንዳንድ አገልግሎቶችን ለግል ጥቅማቸው ያውላሉ፤ አልፎ ተርፎም ገንዘብ ይሰርቃሉ። በተጨማሪም ጓደኞቻቸውንና ዘመዶቻቸውን ለመርዳት ሲሉ ሥልጣናቸውን አላግባብ ይጠቀሙበታል።

ሙስና በማንኛውም ሰብዓዊ ድርጅት ውስጥ ሊኖር ቢችልም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ግን እጅግ ተስፋፍቶ ይገኛል። በመላው ዓለም ያሉ ብዙ ሰዎች እጅግ ሙሰኛ እንደሆኑ አድርገው የሚፈርጇቸው አምስት ተቋማት የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ፖሊስ፣ የሕዝብ ባለሥልጣናት፣ ሕግ አውጪዎችና ዳኞች መሆናቸውን ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም በ2013 ያወጣው ግሎባል ኮራፕሽን ባሮሜትር የተሰኘው ጽሑፍ ዘግቧል። ችግሩን አጉልተው የሚያሳዩ ጥቂት ዘገባዎችን እስቲ ተመልከት፦

  • አፍሪካ፦ በ2013፣ በደቡብ አፍሪካ 22,000 ያህል የሕዝብ ባለሥልጣናት በሙስና ተከሰው ነበር።

  • ደቡብ አሜሪካ፦ በ2012 በብራዚል 25 ባለሥልጣናት ፖለቲካዊ ድጋፍ ለማግኘት ሲሉ የሕዝብን ገንዘብ አላግባብ ጥቅም ላይ በማዋላቸው ተፈርዶባቸው ነበር። ከተፈረደባቸው ሰዎች መካከል በአገሪቱ ውስጥ ሁለተኛውን ከፍተኛ ሥልጣን የያዙት ግለሰብ ይኸውም የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዋና ሹም ይገኙበታል።

  • እስያ፦ በደቡብ ኮሪያ፣ ሶል ከተማ ውስጥ በ1995 አንድ የገበያ አዳራሽ ተደርምሶ 502 ሰዎች ሞተው ነበር። የገበያ አዳራሹን የገነቡት ሕንፃ ተቋራጮች ለከተማዋ ባለሥልጣናት ጉቦ በመስጠት የጥራት ደረጃውን ባልጠበቀ የግንባታ ዕቃ እንደተጠቀሙና አንድ ሕንፃ እንዲያሟላቸው የሚጠበቁ የደኅንነት ደንቦችን እንደተላለፉ ጉዳዩን የያዙት መርማሪዎች ደርሰውበታል።

  • አውሮፓ፦ የአውሮፓ አገራት የውስጥ ጉዳይ ኮሚሽነር የሆኑት ሲሲሊያ ማልምስትሮም እንደገለጹት ከሆነ “[በአውሮፓ የሙስና] ችግር በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተስፋፋ መጥቷል።” እኚህ ሴት አክለው “የፖለቲካው ሥርዓት፣ ሙስናን ከሥሩ ነቅሎ ለማስወገድ የሚያስችል ጥንካሬ የጎደለው ይመስላል” በማለት ተናግረዋል።

ሙስና በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ሥር የሰደደ ችግር ነው። ከፀረ ሙስና ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የሚያጠኑት ፕሮፌሰር ሱዛን ሮዝአከርማን፣ ሙስናን ለማስወገድ “በመንግሥት አሠራር ላይ መሠረታዊ ለውጥ ማድረግ” እንደሚያስፈልግ ጽፈዋል። ሁኔታው ተስፋ አስቆራጭ ይመስል ይሆናል፤ መጽሐፍ ቅዱስ ግን ከዚህም የሚበልጡ ለውጦችን ማድረግ እንደሚቻልና ይህ መሆኑም እንደማይቀር ይገልጻል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ