የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w15 12/1 ገጽ 16
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • እውነት ጊዜ ያለፈበት ነገር ሆኗል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ክርስቲያኖች አምላክን በመንፈስና በእውነት ያመልካሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • የእውነትን አምላክ መምሰል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2003
  • አምላክን መስማት የምንችለው እንዴት ነው?
    አምላክን ስማ የዘላለም ሕይወት ታገኛለህ
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
w15 12/1 ገጽ 16

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው

አምላክን በተመለከተ እውነቱን ማወቅ እንችላለን?

አንድ የይሖዋ ምሥክር መናፈሻ ውስጥ አግዳሚ ወንበር ላይ ለተቀመጠ ሰው ሲሰብክ

አምላክ እውነትን እንድናውቅ የሚፈልገው ለምንድን ነው? ዮሐንስ 17:3ን አንብብ

አምላክ ሐሳቡን ለሰው ልጆች ገልጿል። ሐሳቡን በመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች አእምሮ ውስጥ ለማስቀመጥ መንፈስ ቅዱስን ወይም በሥራ ላይ ያለው ኃይሉን ተጠቅሟል። (2 ጴጥሮስ 1:20, 21) መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ ስለ አምላክ እውነቱን ማወቅ እንችላለን።—ዮሐንስ 17:17ን እና 2 ጢሞቴዎስ 3:16ን አንብብ።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አምላክ ስለ ራሱ ብዙ ነገር ገልጾልናል። ሰዎችን የፈጠረው ለምን እንደሆነ፣ ወደፊት ለሰው ልጆች ምን እንደሚያደርግላቸው እንዲሁም ምን ዓይነት ሕይወት እንድንመራ እንደሚፈልግ አሳውቆናል። (የሐዋርያት ሥራ 17:24-27) ይሖዋ አምላክ ስለ እሱ እውነቱን እንድናውቅ ይፈልጋል።—1 ጢሞቴዎስ 2:3, 4ን አንብብ።

አምላክ እውነት ወዳድ የሆኑ ሰዎች ወደ እሱ እንዲመጡ የሚያደርገው ለምንድን ነው?

ይሖዋ የእውነት አምላክ ነው፤ ደግሞም ለሰው ልጆች እውነትን እንዲያስተምር ልጁን ኢየሱስን ወደ ምድር ልኮታል። በመሆኑም እውነትን የሚወዱ ሰዎች የኢየሱስን ትምህርት ይቀበላሉ። (ዮሐንስ 18:37) አምላክ እንዲህ ያሉ ሰዎች እሱን እንዲያመልኩት ይፈልጋል።—ዮሐንስ 4:23, 24ን አንብብ።

ሰይጣን ዲያብሎስ አምላክን በተመለከተ የሐሰት ትምህርቶች በማስፋፋት ብዙ ሰዎች አምላክን እንዳያውቁ አድርጓል። (2 ቆሮንቶስ 4:3, 4) መልካም የሆነውን ነገር የማይወዱ ሰዎች እንዲህ ላሉ የሐሰት ትምህርቶች ጆሮ ይሰጣሉ። (ሮም 1:25) ሆኖም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን በማጥናት ስለ አምላክ እውነቱን እየተማሩ ነው።—የሐዋርያት ሥራ 17:11ን አንብብ።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በይሖዋ ምሥክሮች የተዘጋጀውን ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የሚል ርዕስ ያለውን የዚህን መጽሐፍ ምዕራፍ 1 ተመልከት

መጽሐፉ www.jw.org/am ላይም ይገኛል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ