የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 5/02 ገጽ 1
  • እምነታችን ለመልካም ሥራ ያነሳሳናል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እምነታችን ለመልካም ሥራ ያነሳሳናል
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ በገባው ቃል ላይ እምነት እንዳላችሁ በተግባር አሳዩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • “እምነት ጨምርልን”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • እምነትህ ምን ያህል ጠንካራ ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2003
  • በእውነት ላይ የተመሠረተ እምነት አሳዩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2002
km 5/02 ገጽ 1

እምነታችን ለመልካም ሥራ ያነሳሳናል

1 ኖኅን፣ ሙሴንና ረዓብን ለድርጊት ያነሳሳቸው እምነት ነው። ኖህ መርከብ ሠርቷል። ሙሴ በፈርዖን ቤተ መንግሥት ውስጥ መኖር የሚያስገኛቸውን ጊዜያዊ ጥቅሞች ትቷል። ረዓብ ሰላዮቹን ደብቃለች፤ ከዚያም ትእዛዛቸውን በመጠበቅ የቤተሰቧን ሕይወት አድናለች። (ዕብ. 11:​7, 24-26, 31) በዛሬው ጊዜስ እምነታችን የሚያነሳሳን ምን ዓይነት መልካም ሥራዎችን እንድንሠራ ነው?

2 መመሥከር፦ እምነት ታላቅ ስለሆነው አምላካችንና ዘላለማዊ ደስታ እንድናገኝ ሲል ስላደረጋቸው ዝግጅቶች እንድንናገር ይገፋፋናል። (2 ቆ⁠ሮ. 4:13) አንዳንድ ጊዜ ከመመሥከር ወደ ኋላ እንል ይሆናል። ይሁን እንጂ ‘ሁልጊዜ ይሖዋ የሚታየን’ ከሆነ ጥንካሬ እናገኛለን፤ ፍርሃታችንም ሁሉ ይጠፋል። (መዝ. 16:8) በዚህ መንገድ እምነታችን ተስማሚ ሆኖ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ለዘመዶቻችን፣ ለጎረቤቶቻችን፣ ለሥራ ባልደረባዎቻችን፣ አብረውን ለሚማሩትና ለሌሎችም ምሥራቹን እንድናካፍል ይገፋፋናል።​—⁠ሮሜ 1:​14-16

3 አብሮ መሰብሰብ፦ ከእምነት የሚመነጨው ሌላው መልካም ሥራ አዘውትሮ በስብሰባ ላይ መገኘት ነው። እንዴት? በክርስቲያናዊ ስብሰባዎች ላይ መገኘታችን ኢየሱስ በአምላክ ቅዱስ መንፈስ አማካኝነት በመካከላችን እንደሚሆን ያለንን ጽኑ እምነት ያሳያል። (ማቴ. 18:​20) “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን” መስማት እንደምንፈልግ ያሳያል። (ራእይ 3:6) እያስተማረን ያለው ታላቁ አስተማሪያችን ይሖዋ መሆኑን በእምነት ዓይናችን ስለምንመለከት የሚሰጠንን ትምህርት በቁም ነገር እንመለከተዋለን።​—⁠ኢሳ. 30:20

4 የምናደርጋቸው ውሳኔዎች፦ በዓይናችን ስለማናያቸው ነገሮች ያለን ጽኑ እምነት በሕይወታችን ውስጥ ለመንፈሳዊ ነገሮች ቅድሚያ እንድንሰጥ ይገፋፋናል። (ዕብ. 11:​1) ይህ አብዛኛውን ጊዜ ቁሳዊ ጥቅማችንን መሥዋዕት ማድረግን ይጠይቃል። ለምሳሌ ያህል አንድ ሽማግሌ ከስብሰባዎች እንዲቀር፣ ከቤተሰቡ እንዲራራቅና የአቅኚነት አገልግሎቱን እንዲያቋርጥ የሚያደርገው ሆኖ ስላገኘው በሰብዓዊ ሥራው የደረጃ እድገት ሊያሰጠው የሚችለውን አጋጣሚ ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። እኛም በተመሳሳይ ‘መንግሥቱንና ጽድቁን ማስቀደማቸውን’ ለሚቀጥሉ ሁሉ ይሖዋ የሚያስፈልጋቸውን ነገር እንደሚያሟላላቸው መጽሐፍ ቅዱስ በሚሰጠው ማረጋገጫ ላይ ሙሉ እምነት ይኑረን።​—⁠ማቴ. 6:​33

5 እምነት በሕይወታችን ላይ ምን ያህል በጎ ተጽዕኖ እንዳሳደረ ሌሎችም መመልከታቸው አይቀርም። ደግሞም እምነታችን በዓለም ዙሪያ የታወቀ ነው። (ሮሜ 1:8) እንግዲያውስ ሁላችንም ሕያው የሆነ እምነት እንዳለን በመልካም ሥራዎቻችን እናሳይ።​—⁠ያዕ. 2:26

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ