የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 4/11 ገጽ 2
  • የጥያቄ ሣጥን

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የጥያቄ ሣጥን
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ‘በእምነት ጸንተው እንዲኖሩ’ እርዷቸው
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2013
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶቻችን እድገት አድርገው እንዲጠመቁ መርዳት—ክፍል ሁለት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶቻችን እድገት አድርገው እንዲጠመቁ መርዳት—ክፍል አንድ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እድገት አድርገው እንዲጠመቁ በጉባኤ ደረጃ መርዳት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2021
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
km 4/11 ገጽ 2

የጥያቄ ሣጥን

◼ ጥሩ እድገት እያደረገ ካለ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ ጋር ማጥናት ያለብን ለምን ያህል ጊዜ ነው?

ጥሩ እድገት እያደረገ ያለ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? እና ‘ከአምላክ ፍቅር አትውጡ’ የተባሉትን ጽሑፎች አጥንቶ እስኪጨርስ ድረስ ማጥናቱን ቢቀጥል የተሻለ ነው። ተማሪው እነዚህን መጻሕፍት አጥንቶ ከመጨረሱ በፊት ቢጠመቅ እንኳ ጥናቱን መቀጠል ይኖርበታል። ግለሰቡ ከተጠመቀም በኋላ ሰዓቱን፣ ተመላልሶ መጠየቆችንና ጥናቱን ሪፖርት ማድረጋችንን መቀጠል እንችላለን። በጥናቱ ወቅት ሌላ አስፋፊ ከተገኘ እሱም ሰዓት መያዝ ይችላል።​—የመጋቢት 2009 የመንግሥት አገልግሎታችንን ገጽ 2 ተመልከት።

አዲሶች ጥናታቸውን ከማቆማቸው በፊት በእውነት ውስጥ ጥሩ መሠረት ሊኖራቸው ይገባል። ወደፊት የሚያጋጥማቸውን መከራ መቋቋም እንዲችሉ በክርስቶስ ላይ ‘መተከልና በእምነት ጸንተው መኖር’ ያስፈልጋቸዋል። (ቆላ. 2:6, 7፤ 2 ጢሞ. 3:12፤ 1 ጴጥ. 5:8, 9) በተጨማሪም ሌሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተማር “የእውነትን ትክክለኛ እውቀት” ማግኘት ያስፈልጋቸዋል። (1 ጢሞ. 2:4) ጥናቶቻችንን ሁለቱንም መጽሐፍ የምናስጠናቸው ከሆነ ‘ወደ ሕይወት ከሚወስደው መንገድ’ እንዳይወጡ እየረዳናቸው ነው።​—ማቴ. 7:14

ሽማግሌዎች አንድ ሰው እንዲጠመቅ ከመፍቀዳቸው በፊት መሠረታዊ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች በሚገባ መረዳቱንና አኗኗሩ ከዚህ ጋር የሚስማማ መሆኑን ማረጋገጥ አለባቸው። ሽማግሌዎች በተለይ የመጀመሪያውን የማጥኛ መጽሐፍ ያልጨረሱ ጥናቶች ለመጠመቅ የሚያቀርቡትን ጥያቄ ሲያዩ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። አንድ ሰው ለመጠመቅ ብቁ ካልሆነ ሽማግሌዎቹ ግለሰቡ ወደፊት ብቁ ለመሆን የሚያስችለውን እርዳታ እንዲያገኝ ሁኔታውን ማመቻቸት ይኖርባቸዋል።​—የይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ፣ ከገጽ 216-218 ተመልከት።

[በገጽ 2 ላይ የሚገኝ የተቀነጨበ ሐሳብ]

አዲሶች . . . በእውነት ውስጥ ጥሩ መሠረት ሊኖራቸው ይገባል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ