የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 11/11 ገጽ 4
  • የአቀራረብ ናሙናዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአቀራረብ ናሙናዎች
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2013
  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ተፈጥሮ አደጋዎች ምን ይላል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • የአቀራረብ ናሙናዎች
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2012
  • የተፈጥሮ አደጋዎች ይህን ያህል የበዙት ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2011
km 11/11 ገጽ 4

የአቀራረብ ናሙናዎች

በወሩ የመጀመሪያ ቅዳሜ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለማስጀመር የሚረዳ አቀራረብ

“ጓደኛ የማያስፈልገው ሰው የለም ቢባል እንደሚስማሙ እርግጠኛ ነኝ። ለጓደኝነት የሚመርጡት ሰው በዋነኛነት ምን ዓይነት ባሕርይ እንዲኖረው ይፈልጋሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ይህ መጽሔት ጓደኞቻችንን በጥበብ መምረጥ የሚኖርብን ለምን እንደሆነ የሚገልጽ ጥሩ ሐሳብ ይዟል።” ከዚያም የታኅሣሥ 1⁠ን መጠበቂያ ግንብ ስጠውና በገጽ 16 ላይ በሚገኘው በመጀመሪያው ንዑስ ርዕስ ሥር ያለውን ሐሳብ አብራችሁ ካነበባችሁ በኋላ ተወያዩበት። በተጨማሪም በንዑስ ርዕሱ ውስጥ ከሚገኙት ጥቅሶች መካከል ቢያንስ አንዱን አንብቡ። መጽሔቶቹን ካበረከትክለት በኋላ በሚቀጥለው ጥያቄ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ያዝ።

ታኅሣሥ 1 መጠበቂያ ግንብ

“ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተፈጥሮ አደጋዎች እየተበራከቱ የመጡት ለምን እንደሆነ አስበው ያውቃሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] የሚገርመው፣ የተፈጥሮ አደጋዎች የሚበዙበት ዘመን እንደሚመጣ መጽሐፍ ቅዱስ አስቀድሞ ተናግሯል። [ማቴዎስ 24:7, 8⁠ን አንብብ።] ይህ መጽሔት ‘በዛሬው ጊዜ የተፈጥሮ አደጋዎች ይህን ያህል የበዙት ለምንድን ነው? እነዚህ አደጋዎች የሚደርሱት አምላክ እየቀጣን ስለሆነ ነው? አምላክ በቅርቡ ማንኛውንም የተፈጥሮ አደጋ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ብለን እንድናምን የሚያደርጉን ምን ምክንያቶች አሉ?’ ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል።”

ታኅሣሥ ንቁ!

2 ጢሞቴዎስ 3:16⁠ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ በል፦ “ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ በአምላክ መንፈስ መሪነት የተጻፈ እንደሆነ የሚያምኑ ቢሆንም አንዳንዶች ግን እንደዚህ አይሰማቸውም። እርስዎስ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላሉ? [ሐሳቡን እንዲገልጽ ዕድል ስጠው።] ሰዎች በዚህ ጉዳይ ላይ ያላቸው አመለካከት የተለያየ ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥፋት በርካታ ሙከራዎች እንደተደረጉና የእሱን ያህል የጥቃት ዒላማ የሆነ መጽሐፍ እንደሌለ ብዙዎች ይስማማሉ። ይህ መጽሔት ባለፉት መቶ ዘመናት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥፋትና ሰዎች እንዳያነቡት ለማገድ የተደረጉ አንዳንድ ጥረቶችን ይገልጻል። በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ከጥፋት ሊተርፍ እንደቻለ ያብራራል።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ