የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w22 የካቲት ገጽ 30
  • ይህን ያውቁ ኖሯል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይህን ያውቁ ኖሯል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ምክንያታዊ የሆነ ጥሎሽ ለመስጠትም ሆነ ለመቀበል መስማማት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1998
  • የተሳካ ትዳር ለመመሥረት መዘጋጀት
    ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
  • ሴቶች በጥንት የአምላክ አገልጋዮች ዘንድ የነበራቸው የተከበረ ቦታ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
  • በትዳራችሁ ተደሰቱ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022
w22 የካቲት ገጽ 30
አንድ እስራኤላዊ ለወደፊት አማቱ የማጫ ዋጋ ለመክፈል ላም ይዞ ሲመጣ።

የማጫ ዋጋ እንስሳም ሊሆን ይችላል

ይህን ያውቁ ኖሯል?

የጥንቶቹ እስራኤላውያን የማጫ ዋጋ ይከፍሉ የነበረው ለምንድን ነው?

በጥንት ዘመን የማጫ ዋጋ፣ አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ለማግባት ሲያስብ ለሙሽሪት ቤተሰብ የሚሰጠው ክፍያ ነው። ንብረት፣ እንስሳት ወይም ገንዘብ በመስጠት ክፍያው ይፈጸም ነበር። የማጫ ዋጋ የጉልበት ሥራ በማከናወንም ሊከፈል ይችላል፤ ለምሳሌ ያዕቆብ ራሔልን ለማግባት ሲል አባቷን ለሰባት ዓመታት ለማገልገል ተስማምቶ ነበር። (ዘፍ. 29:17, 18, 20) የዚህ ባሕል ዓላማ ምን ነበር?

የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር የሆኑት ካሮል ማየርዝ እንዲህ ብለዋል፦ “[በግብርና በሚተዳደር] ቤተሰብ ውስጥ ሴት ልጅ የምታከናውነው ሥራ በጣም አስፈላጊ ነው፤ በመሆኑም የማጫ ዋጋ ሴት ልጃቸውን ለሰጡት የሙሽሪት ቤተሰብ ማካካሻ ይሆናል።” በተጨማሪም የማጫ ዋጋ በጋብቻ የተሳሰሩትን ቤተሰቦች ወዳጅነት ያጠናክራል። እንዲህ ያለው ወዳጅነት ደግሞ በችግር ጊዜ ለመረዳዳት ይጠቅማል። በተጨማሪም የማጫ ዋጋ፣ አንዲት ሴት እንደታጨች እንዲሁም እንክብካቤና ጥበቃ ተደርጎላት ካደገችበት የአባቷ ቤት ወጥታ ወደ ባሏ ቤት ልትሸኝ መሆኑን ያረጋግጣል።

የማጫ ዋጋ መክፈል፣ ሚስት የምትሸጥ ወይም የምትለወጥ ንብረት ተደርጋ እንደምትቆጠር የሚያሳይ አይደለም። ኤንሸንት ኢዝራኤል—ኢትስ ላይፍ ኤንድ ኢንስትቲውሽንስ የተባለው መጽሐፍ እንዲህ ይላል፦ “ሙሽራው ለሙሽሪት ቤተሰብ ገንዘብ ወይም ሌላ ተመጣጣኝ ነገር እንዲከፍል መገደዱ ላይ ላዩን ሲታይ እስራኤላውያን ሴት ልጅን ንብረት አድርገው የሚቆጥሩ ሊያስመስል ይችላል። ሆኖም [የማጫ ዋጋ] ለቤተሰቧ የሚሰጥ ካሳ እንጂ ልጅቷን ለመግዛት የሚከፈል ዋጋ ተደርጎ ሊቆጠር አይገባም።”

በዛሬው ጊዜም በአንዳንድ አገሮች የማጫ ዋጋ የመክፈል ባሕል አለ። ክርስቲያን ወላጆች ከሚገባው በላይ የማጫ ዋጋ መጠየቅ የለባቸውም፤ በዚህ መንገድ “ምክንያታዊነታችሁ በሰው ሁሉ ዘንድ የታወቀ ይሁን” የሚለውን መሠረታዊ ሥርዓት እንደሚከተሉ ያሳያሉ። (ፊልጵ. 4:5፤ 1 ቆሮ. 10:32, 33) ይህን ማድረጋቸው “ገንዘብ የሚወዱ” ወይም ስግብግቦች እንዳልሆኑም ያሳያል። (2 ጢሞ. 3:2) በተጨማሪም ባልየው የሙሽሪት ወላጆች የጠየቁትን የተጋነነ ዋጋ ሠርቶ እስኪያገኝ ድረስ የሠርጉን ቀን ለማራዘም አይገደድም። ባልየው አቅኚ ከሆነም የተጠየቀውን ከፍተኛ ዋጋ ለመክፈል ሲል ‘አቅኚነቴን አቁሜ የሙሉ ቀን ሥራ ልሥራ’ ብሎ አያስብም።

በአንዳንድ የዓለም ክፍሎች የማጫ ዋጋን የሚተምን ሕግ አለ። በእነዚህ ቦታዎች የሚኖሩ ክርስቲያን ወላጆች ለእነዚህ ሕጎች ይታዘዛሉ። ለምን? ምክንያቱም ክርስቲያኖች “ለበላይ ባለሥልጣናት [እንድንገዛ]” እንዲሁም የሚያወጧቸው ሕጎች ከአምላክ ሕጎች ጋር የሚጋጩ እስካልሆኑ ድረስ እንድንታዘዛቸው የአምላክ ቃል ያዘናል።—ሮም 13:1፤ ሥራ 5:29

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ