የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w24 ሰኔ ገጽ 32
  • እምነት አለህ?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እምነት አለህ?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ በገባው ቃል ላይ እምነት እንዳላችሁ በተግባር አሳዩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • “እምነት ጨምርልን”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • እምነት—በመንፈሳዊ የሚያጠነክር ባሕርይ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
  • በእውነት ላይ የተመሠረተ እምነት አሳዩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
w24 ሰኔ ገጽ 32

የመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ

እምነት አለህ?

ይሖዋን ማስደሰት ከፈለግን እምነት ሊኖረን ይገባል። ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ “እምነት ሁሉም ሰው የሚኖረው ነገር አይደለም” ይላል። (2 ተሰ. 3:2) እዚህ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ እየተናገረ ያለው እያሳደዱት ስላሉት ‘መጥፎና ክፉ ሰዎች’ ነው። ሆኖም ስለ እምነት የተናገረው ሐሳብ የሚሠራው ለእነዚህ ሰዎች ብቻ አይደለም። አንዳንዶች ሁሉንም ነገር የፈጠረ አምላክ መኖሩን የሚያሳየውን ግልጽ ማስረጃ ሆን ብለው ይክዳሉ። (ሮም 1:20) ሌሎች ደግሞ ከሰዎች የበለጠ ኃይል ያለው አካል መኖሩን እንደሚያምኑ ይናገሩ ይሆናል። ሆኖም ይህን ማመን ብቻውን ይሖዋን ለማስደሰት በቂ አይደለም።

ይሖዋ መኖሩንና ጠንካራ እምነት ላላቸው ሰዎች ወሮታ ከፋይ መሆኑን እርግጠኛ ልንሆን ይገባል። (ዕብ. 11:6) እምነት የአምላክ ቅዱስ መንፈስ ፍሬ አንድ ገጽታ ነው። አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስን ለማግኘት ወደ ይሖዋ መጸለይ አለበት። (ሉቃስ 11:9, 10, 13) ይህን መንፈስ ለማግኘት የሚረዳን አንዱ ወሳኝ ነገር በመንፈስ መሪነት የተጻፈውን የአምላክን ቃል ማንበብ ነው። ከዚያም ባነበብነው ነገር ላይ ማሰላሰልና ያገኘነውን ትምህርት በሥራ ላይ ለማዋል ጥረት ማድረግ እንችላለን። እንዲህ ካደረግን የይሖዋ መንፈስ እሱን የሚያስደስት ዓይነት እምነት እንዳለን በሚያሳይ መንገድ ሕይወታችንን ለመምራት ይረዳናል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ