የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w25 መጋቢት ገጽ 32
  • መስተዋቱን በደንብ ተጠቀሙበት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መስተዋቱን በደንብ ተጠቀሙበት
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ እኔን የሚመለከተኝ እንዴት ነው?
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2014
  • የራስን ጥቅም የመሠዋትን መንፈስ ይዘን መቀጠል የምንችለው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
  • የምትናገረው ነገር ለውጥ ያመጣል?
    ንቁ!—2011
  • ስለ መልካችሁ ሚዛናዊ አመለካከት መያዝ
    ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
w25 መጋቢት ገጽ 32

ለጥናት የሚረዱ ሐሳቦች

መስተዋቱን በደንብ ተጠቀሙበት

ደቀ መዝሙሩ ያዕቆብ መጽሐፍ ቅዱስን ከመስተዋት ጋር አመሳስሎታል፤ ውስጣዊ ማንነታችንን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። (ያዕ. 1:22-25) ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ እንደ መስተዋት እንዲያገለግለን እንዴት አድርገን ልንጠቀምበት ይገባል?

በጥሞና አንብቡ። መስተዋት ላይ ራሳችንን የምናየው እንዲሁ ገረፍ አድርገን ከሆነ ጎልቶ የሚታይ እንከን እንኳ ሊያልፈን ይችላል። በተመሳሳይም ውስጣዊ ማንነታችን ላይ መታረም ያለበት ነገር እንዲታየን የአምላክን ቃል በጥሞና ማንበብ አለብን።

ከሌሎች ይልቅ ራሳችሁን ተመልከቱ። መስተዋቱን የያዝነው ከእኛ ትይዩ ሳይሆን ጋደል አድርገን ከሆነ የሌላ ሰው እንከን ሊታየን ይችላል። በተመሳሳይም መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ የሌሎችን እንከን ማሰብ ይቀናን ይሆናል። ይህ ግን እኛ ማስተካከል ያለብን ነገር ላይ እንዳናተኩር ያደርገናል።

ምክንያታዊ ሁኑ። መስተዋት ላይ የሚታየን እንከናችን ብቻ ከሆነ ተስፋ ሊያስቆርጠን ይችላል። በመሆኑም የአምላክን ቃል ስናነብ ምክንያታዊ መሆን አለብን፤ ይሖዋ ከእኛ ከሚጠብቀው በላይ ከራሳችን መጠበቅ አይኖርብንም።—ያዕ. 3:17

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ