የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mrt ርዕስ 109
  • ኢየሱስ ወንጀልን ያስወግዳል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢየሱስ ወንጀልን ያስወግዳል
  • ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ኢየሱስ ድህነትን ያስወግዳል
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ኢየሱስ ጦርነትን ያስወግዳል
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ማንን ማመን ትችላለህ?—መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ሥርዓት አልበኝነት በዓለም ዙሪያ ጨምሯል—መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
ለተጨማሪ መረጃ
ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
mrt ርዕስ 109
አንድ ወንጀለኛ ብቻዋን ያለችን አንዲት ሴት ሲከታተላት። ሴትየዋ ወንጀለኛውን ከኋላዋ ስታየው ሞባይሏን አውጥታ እርዳታ ለመጠየቅ ትሞክራለች።

alfa27/stock.adobe.com

ኢየሱስ ወንጀልን ያስወግዳል

ኢየሱስ የወንጀልና የግፍ ሰለባ መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ በሚገባ ይረዳል። በሐሰት ተከሷል፤ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ተደብድቧል፤ ያለጥፋቱ ተፈርዶበታል እንዲሁም በሚያሠቃይ ሁኔታ ተገድሏል። ምንም ኃጢአት ባይሠራም ‘በብዙዎች ምትክ ሕይወቱን ቤዛ አድርጎ ሰጥቷል።’ (ማቴዎስ 20:28፤ ዮሐንስ 15:13) አሁን የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሆኖ እየገዛ ሲሆን በቅርቡ ወንጀልን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በማስወገድ በመላው ምድር ላይ ፍትሕ እንዲሰፍን ያደርጋል።​—ኢሳይያስ 42:3

መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ እርምጃ ከወሰደ በኋላ ዓለማችን ምን መልክ እንደሚኖራት ሲገልጽ እንዲህ ይላል፦

  • “ክፉዎች አይኖሩም፤ በቀድሞ ቦታቸው ትፈልጋቸዋለህ፤ እነሱ ግን በዚያ አይገኙም። የዋሆች ግን ምድርን ይወርሳሉ፤ በብዙ ሰላምም እጅግ ደስ ይላቸዋል።”​—መዝሙር 37:10, 11

ኢየሱስ ላደረገልን ነገር እንዲሁም ወደፊት ለሚያደርግልን ነገር ያለንን አድናቆት ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው? አንዱ መንገድ ‘ስለ አምላክ መንግሥት ምሥራች’ መማር ነው፤ ኢየሱስ የሰበከው ስለዚህ መንግሥት ነበር። (ሉቃስ 4:43) “የአምላክ መንግሥት ምንድን ነው?” የሚለውን ርዕስ እንድታነብ እንጋብዝሃለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ