የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • sn መዝ. 33
  • አትፍሯቸው!

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አትፍሯቸው!
  • ለይሖዋ ዘምሩ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አትፍሯቸው!
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ይሖዋን ፍሩ ቅዱስ ስሙንም አክብሩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1992
  • ይሖዋን የሚፈራ ልብ ይኑርህ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ይሖዋን በመፍራት ደስታ ማግኘትን መማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
ለይሖዋ ዘምሩ
sn መዝ. 33

መዝሙር 33

አትፍሯቸው!

በወረቀት የሚታተመው

(ማቴዎስ 10:28)

1. ሕዝቦቼ ወደፊት ግፉ፤

ምሥራቹን አስፋፉ።

አትፍሩ ጠላቶችን።

አሳውቁ ቅኖችን፣

ልጄ ክርስቶስ መንገሡን፣

ጠላቱን መወርወሩን፤

በቅርቡም ሰይጣንን ያስራል፤

ምርኮኞችን ያስፈታል።

(አዝማች)

አትፍሩ የኔ ወዳጆች፤

ቢዝቱ ’ንኳ ጠላቶች።

’ጠብቃለሁ ታማኞቼን፤

ልክ እንደ ዓይኔ ብሌን።

2. ጠላቶቻችሁ ቢበዙም፣

ቢዝቱ፣ ቢሳደቡም፣

ለመሸንገል ቢጥሩ፣

ለማሳት ቢሞክሩ፣

ባሮቼ አትሸበሩ፤

ቢቃወሙም አትፍሩ።

ድል እስኪገኝ ባርማጌዶን፣

አልጥልም ታማኞችን።

(አዝማች)

አትፍሩ የኔ ወዳጆች፤

ቢዝቱ ’ንኳ ጠላቶች።

’ጠብቃለሁ ታማኞቼን፤

ልክ እንደ ዓይኔ ብሌን።

3. አትስጉ አልተዋችሁም፤

ጋሻችሁ ነኝ አሁንም።

በስደት ብትሞቱም፣

ሞታችሁ አትቀሩም።

ነፍስን መግደል ’ማይችሉትን

ፈጽሞ አትፍሯቸው።

ባቋማችሁ ከጸናችሁ

ሕይወት ታገኛላችሁ!

(አዝማች)

አትፍሩ የኔ ወዳጆች፤

ቢዝቱ ’ንኳ ጠላቶች።

’ጠብቃለሁ ታማኞቼን፤

ልክ እንደ ዓይኔ ብሌን።

(በተጨማሪም ዘዳ. 32:10⁠ን፣ ነህ. 4:14⁠ን፣ መዝ. 59:1⁠ን እና መዝ. 83:2, 3⁠ን ተመልከት።)

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ