የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • sn መዝ. 10
  • “እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • “እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”
  • ለይሖዋ ዘምሩ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • “እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • መጨረሻ የሌለው ሕይወት
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ለአገልግሎት መዘጋጀት
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ለአገልግሎት መዘጋጀት
    ለይሖዋ ዘምሩ—አዲስ መዝሙሮች
ለተጨማሪ መረጃ
ለይሖዋ ዘምሩ
sn መዝ. 10

መዝሙር 10

“እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”

በወረቀት የሚታተመው

(ኢሳይያስ 6:8)

1. አምላክ ዛሬ ስሙ ጠፍቷል፤

ጨካኝ ተደርጎ ተቆጥሯል።

‘ደካማ ነው’ ብለውታል፤

ሞኝም “አምላክ የለም” ይላል።

ማን ነው ጥብቅና ’ሚቆመው?

አምላክን የሚያወድሰው?

“ጌታ ’ነሆኝ! እኔን ላከኝ፤

ለመናገር ድፍረት አለኝ።

(አዝማች)

ከዚህ በላይ ምን ክብር ሊገኝ፤

እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”

2. አይፈሩም ሲገዳደሩት፣

‘እርምጃ አይወስድም’ ሲሉት።

ጣዖት ሠርተው አመለኩ፤

ቦታውን በቄሳር ተኩ።

ማን ሄዶ ያስጠንቅቃቸው?

“ጥፋት መጣ” ይበላቸው?

“ጌታ ’ነሆኝ! እኔን ላከኝ፤

አሰማለሁ ውዳሴህን።

(አዝማች)

ከዚህ በላይ ምን ክብር ሊገኝ፤

እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”

3. ዓለም በክፋት ተሞልቷል፤

ገሮች አዝነው አልቅሰዋል።

ሰላም ’ሚሰጠውን እውነት፣

ያስፈልጋቸዋል ማግኘት።

ማን ነው ሄዶ ’ሚያጽናናቸው?

መንገዱን የሚያሳያቸው?

“ጌታ ’ነሆኝ! እኔን ላከኝ፤

ለማስተማር ት’ግሥት አለኝ።

(አዝማች)

ከዚህ በላይ ምን ክብር ሊገኝ፤

እነሆኝ! እኔን ላከኝ!”

(በተጨማሪም መዝ. 10:4⁠ን እና ሕዝ. 9:4⁠ን ተመልከት።)

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ