የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • sjj መዝ. 155
  • የዘላለም ደስታ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የዘላለም ደስታ
  • ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ደስታ—ከአምላክ የምናገኘው ግሩም ባሕርይ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • አዲሱን የምድር ንጉሥ አወድሱ
    ለይሖዋ ዘምሩ
  • እውነትን የራስህ አድርግ
    ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
  • እውነትን የራስህ አድርግ
    ለይሖዋ ዘምሩ
ለተጨማሪ መረጃ
ለይሖዋ ‘በደስታ ዘምሩ’
sjj መዝ. 155

መዝሙር 155

የዘላለም ደስታ

በወረቀት የሚታተመው

(መዝሙር 16:11)

  1. 1. ሰማያትን የዘረጋህ

    ታላቁ ጌታ፣

    ውብ አድርገህ ሠራሃቸው

    ፀሐይ፣ ጨረቃን።

    ምድርን ሠርተህ አሳምረህ፣

    ስታበቃ ሁሉን ፈጥረህ፣

    ደስ አለው ልብህ።

    (አዝማች)

    ደስ አለን በ’ጆችህ ሥራ፣

    በምናውጀው ምሥራች፣

    ለኛ ባሰብከው ተስፋ።

    ከዚህ ሁሉ ግን ’ሚበልጠው

    በፍቅርህ መኖራችን ነው።

    አንተ ነህ የኛ ደስታ፣

    የዘላለም ደስታ።

  2. 2. ሁሉን ነገር ሰጥተኸናል

    ለጋሱ ጌታ፤

    ልባችን ሐሴት ያደርጋል

    ባንተ ስጦታ።

    ፈጥረኸናል በአምሳልህ

    ግሩም አድርገህ በፍቅርህ፤

    ድንቅ ነው ሥራህ።

    (አዝማች)

    ደስ አለን በ’ጆችህ ሥራ፣

    በምናውጀው ምሥራች፣

    ለኛ ባሰብከው ተስፋ።

    ከዚህ ሁሉ ግን ’ሚበልጠው

    በፍቅርህ መኖራችን ነው።

    አንተ ነህ የኛ ደስታ፣

    የዘላለም ደስታ።

    (መሸጋገሪያ)

    ልጅህ ሞቶልን ነው

    ከፍለህልን ውድ ዋጋ፤

    የታደልነው ለዚህ ደስታ

    ባንተ ነው፣ ባንተ ውለታ።

    (አዝማች)

    ደስ አለን በ’ጆችህ ሥራ፣

    በምናውጀው ምሥራች፣

    ለኛ ባሰብከው ተስፋ።

    ከዚህ ሁሉ ግን ’ሚበልጠው

    በፍቅርህ መኖራችን ነው።

    አንተ ነህ የኛ ደስታ፣

    የዘላለም ደስታ።

    (አዝማች)

    ደስ አለን በ’ጆችህ ሥራ፣

    በምናውጀው ምሥራች፣

    ለኛ ባሰብከው ተስፋ።

    ከዚህ ሁሉ ግን ’ሚበልጠው

    በፍቅርህ መኖራችን ነው።

    አንተ ነህ የኛ ደስታ፣

    የዘላለም ደስታ።

(በተጨማሪም መዝ. 37:4⁠ን እና 1 ቆሮ. 15:28⁠ን ተመልከት።)

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ