የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • g 1/11 ገጽ 3
  • ሃይማኖት ለሰላም የቆመ ኃይል ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሃይማኖት ለሰላም የቆመ ኃይል ነው?
  • ንቁ!—2011
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በግጭት የተሞላ ታሪክ
  • ለአንድ “ቅዱስ” ሥፍራ መፋለም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1999
  • የዓለም ሃይማኖቶች የሚጠፉት ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1996
  • ተጠያቂው ሃይማኖት ነው?
    ንቁ!—2011
  • ብዙዎች ሃይማኖት ለሰው ዘር አንድነት ሊያስገኝ መቻሉን የሚጠራጠሩት ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
ለተጨማሪ መረጃ
ንቁ!—2011
g 1/11 ገጽ 3

ሃይማኖት ለሰላም የቆመ ኃይል ነው?

በኢየሩሳሌም የሚገኘውን ቅዱስ ሴፐልከር ቤተ ክርስቲያን አንዳንዶች ከአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እጅግ ቅዱስ አድርገው ቢያዩትም ሌሎች ደግሞ የግጭትና የጥላቻ ተምሳሌት አድርገው ይመለከቱታል። አፈ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ይህ ቤተ ክርስቲያን “ክርስቶስ የተገደለበትና ከሞት የተነሳበት ስፍራ እንደሆነ ተደርጎ በሚታሰብ ቦታ ላይ የተገነባ” ነው። ይሁን እንጂ እንደ ቅዱስ የሚታየው ይህ ቦታ በርካታ ግጭቶችንም አስተናግዷል። ክርስቲያን ነን የሚሉ ስድስት ቡድኖች ቤተ ክርስቲያኑን ከመጠቀም መብት ጋር በተያያዘ ለረጅም ጊዜ እርስ በርስ ሲጋጩ ኖረዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ በመካከላቸው ያለው ግጭት ተባብሷል። እንዲያውም በአንድ ወቅት መሣሪያ የታጠቁ ፖሊሶች በተከሰተው ግጭት ውስጥ ጣልቃ ገብተው ቤተ ክርስቲያኑን ለተወሰነ ጊዜ መቆጣጠር ግድ ሆኖባቸው ነበር።

በግጭት የተሞላ ታሪክ

በቅዱስ ሴፐልከር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተከሰቱት ነገሮች በደም መፋሰስና በጭፍጨፋ የተሞላው ረጅም ዘመን ያስቆጠረው የሃይማኖት ታሪክ ክፍል ናቸው። ቫዮለንስ ኢን ጎድስ ኔም የተሰኘው መጽሐፍ በቅርብ ጊዜ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተከሰቱ ግጭቶችን አስመልክቶ ባቀረበው ግምገማ ላይ እንዲህ ብሏል፦ “ከኢንዶኔዥያ እስከ ሰሜን አየርላንድ፣ ከመካከለኛው ምሥራቅ እስከ ካሽሚር፣ ከሕንድ እስከ ናይጄሪያ፣ ከባልካን አገሮች እስከ ስሪ ላንካ፣ ክርስቲያኖች፣ ቡዲስቶች፣ አይሁዶች፣ ሂንዱዎች፣ ሙስሊሞችና ሲኮች ለምን ግጭት ውስጥ እንደገቡ ሰበብ ሲያቀርቡ ሃይማኖታቸውንና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ እንደሆነ ይናገራሉ።”

ሆኖም አብዛኞቹ ሃይማኖቶች መሠረታዊ መመሪያቸው ሰላምና ስምምነት እንደሆነ ይናገራሉ። በዘመናት ሁሉ ሃይማኖቶች ሰውን መውደድንና ለሰው ሕይወት አክብሮት ማሳየትን የመሳሰሉ ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆኑ መርሆዎችን ሲሰብኩ ኖረዋል። ታዲያ ሃይማኖት ከፍተኛ ተጽዕኖ የማሳደር ኃይሉን ሰላም ለማምጣት መጠቀም አይገባውም ነበር? ቅን ልቦና ያላቸው ሃይማኖተኞች በዚህ ጉዳይ ላይ ቆም ብለው እንዲያስቡ እናበረታታቸዋለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ