የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp16 ቁጥር 3 ገጽ 3
  • የምትወደውን ሰው በሞት ስታጣ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የምትወደውን ሰው በሞት ስታጣ
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሌሎች መርዳት የሚችሉት እንዴት ነው?
    የምትወዱት ሰው ሲሞት
  • “ከሚያለቅሱ ጋር አልቅሱ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • ከሐዘኔ ልጽናና የምችለው እንዴት ነው?
    የምትወዱት ሰው ሲሞት
  • የደረሰብህን ሐዘን መቋቋም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
wp16 ቁጥር 3 ገጽ 3
እያለቀሰች ያለች ሴት

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ

የምትወደውን ሰው በሞት ስታጣ

“የኔ ፍቅር . . . አምላክ የተሻለውን ነገር ስለሚያውቅ . . . በቃ አታልቅሺ።”

አንዲት ሴት ወደ ቤቤ ጠጋ ብላ ይህን ሐሳብ በጆሮዋ ሹክ አለቻት። በዚህ ወቅት ቤቤ፣ በመኪና አደጋ ሕይወቱ ባለፈው የአባቷ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ነበረች።

ቤቤ ከአባቷ ጋር በጣም ትዋደድ ነበር። መግቢያው ላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ በአሳቢነት ተነሳስታ የተናገረችው የቤቤ የቅርብ ወዳጅ ብትሆንም ንግግሩ ቤቤን ከማጽናናት ይልቅ ጎዳት። ቤቤ “አባባ ባይሞት ይሻል ነበር” እያለች ታጉተመትም ነበር። ከዓመታት በኋላ ቤቤ በጻፈችው መጽሐፍ ላይ ይህን ገጠመኝ ማውሳቷ በዚህ ጊዜም ቢሆን ሐዘኑ እንዳልወጣላት በግልጽ ያሳያል።

ቤቤ በራሷ ሕይወት እንደተመለከተችው፣ አንድ ሐዘንተኛ በተለይ ከሟቹ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ከነበረው ከሐዘኑ ለመጽናናት ረጅም ጊዜ ሊወስድበት ይችላል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሞት “የመጨረሻው ጠላት” ተብሎ መጠራቱ የተገባ ነው። (1 ቆሮንቶስ 15:26) ሞት ልንቋቋመው በማንችለው ሁኔታ ሕይወታችንን የሚያመሰቃቅልብን ከመሆኑም ሌላ አብዛኛውን ጊዜ ባልጠበቅነው ሰዓት በጣም የምንወዳቸውን ሰዎች ይነጥቀናል። ሞት ከሚያስከትለው ከባድ ጉዳት ማምለጥ የሚችል የለም። በመሆኑም የምንወደውን ሰው በሞት በማጣታችን የተነሳ ግራ ብንጋባ የሚያስገርም አይደለም።

ምናልባት እንዲህ የሚሉ ጥያቄዎች ተፈጥረውብህ ይሆናል፦ ‘ሐዘኑን ለመርሳት ምን ያህል ጊዜ ይፈጅብኛል? አንድ ሰው ከደረሰበት ሐዘን መጽናናት የሚችለው እንዴት ነው? ሐዘን የደረሰባቸውን ሰዎች ለማጽናናት ምን ማድረግ እችላለሁ? በሞት ያጣናቸው የምንወዳቸው ሰዎች ምን ተስፋ አላቸው?’

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ