የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp16 ቁጥር 6 ገጽ 16
  • መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምራል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምራል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አምላክ ለሁሉም ጸሎቶች መልስ ይሰጣል?
  • መጸለይ ያለብን እንዴት ሆነን ነው?
  • ወደ አምላክ የመጸለይ ውድ መብት
    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?
  • በጸሎት አማካኝነት ከአምላክ ጋር ያለህን ዝምድና አጠናክር
    ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
  • አምላክ ለጸሎቴ መልስ ይሰጣል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • በጸሎት አማካኝነት ከአምላክ ጋር መቀራረብ
    አምላክ ከእኛ የሚፈልገው ምንድን ነው?
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
wp16 ቁጥር 6 ገጽ 16
አንዲት ሴት ስትጸልይ

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምራል?

አምላክ ለሁሉም ጸሎቶች መልስ ይሰጣል?

የእነማንን ጸሎት የሚመልስ ይመስልሃል?

  • የሁሉንም ሰዎች

  • የአንዳንድ ሰዎችን

  • የማንንም አይመልስም

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

“ይሖዋ . . . በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።”—መዝሙር 145:18

መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ሌላስ ነገር አለ?

  • አምላክ በእሱ ላይ የሚያምፁ ሰዎችን ጸሎት አይሰማም። (ኢሳይያስ 1:15) ሆኖም መንገዳቸውን በማስተካከል ከአምላክ ጋር ያላቸውን ዝምድና ያበላሸባቸውን ‘ችግር መፍታት’ ይችላሉ።—ኢሳይያስ 1:18

  • አምላክ መልስ የሚሰጠው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሚገኙት መሥፈርቶች ጋር ለሚስማሙ ጸሎቶች ነው።—1 ዮሐንስ 5:14

መጸለይ ያለብን እንዴት ሆነን ነው?

ሰዎች ምን ብለው ያምናሉ? አንዳንድ ሰዎች በሚጸልዩበት ጊዜ ሁሉ መንበርከክ፣ ማጎንበስ ወይም እጃቸውን ማጋጠም እንዳለባቸው ይሰማቸዋል። አንተ ምን ይመስልሃል?

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

አምላክ የተለያዩ ሰዎች ‘ተቀምጠው’ ወይም “ተነስተው፣” አሊያም ‘ተደፍተው’ ወይም ‘ተንበርክከው’ ያቀረቡትን ጸሎት ሰምቷል። (1 ዜና መዋዕል 17:16፤ 2 ዜና መዋዕል 30:27፤ ዕዝራ 10:1፤ የሐዋርያት ሥራ 9:40) በመሆኑም እንዴትም ሆነን ብንጸልይ ለአምላክ ለውጥ አያመጣም።

መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ሌላስ ነገር አለ?

  • አምላክ ትሑት የሆኑ ሰዎችን ጸሎት ይሰማል።—መዝሙር 138:6

  • በማንኛውም ቋንቋ ሌላው ቀርቶ ድምፅ ሳታወጣም መጸለይ ትችላለህ።—2 ዜና መዋዕል 6:32, 33፤ ነህምያ 2:1-6

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በይሖዋ ምሥክሮች የተዘጋጀውን ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የሚል ርዕስ ያለውን የዚህን መጽሐፍ ምዕራፍ 17 ተመልከት

መጽሐፉ www.jw.org/am ላይም ይገኛል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ