የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 9:20, 21
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 20 ኖኅም ገበሬ ሆነ፤ የወይን እርሻም አለማ። 21 አንድ ቀን ኖኅ የወይን ጠጅ ጠጥቶ ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ራቁቱን ሆነ።

  • ምሳሌ 23:29-35
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 29 ዋይታ የማን ነው? ጭንቀት የማን ነው?

      ጠብ የማን ነው? እሮሮ የማን ነው?

      ያለምክንያት መቁሰል የማን ነው? የዓይን ቅላት* የማን ነው?

      30 ይህ ሁሉ የሚደርሰው የወይን ጠጅ በመጠጣት ረጅም ጊዜ በሚያሳልፉ፣+

      የተደባለቀም ወይን ጠጅ ፍለጋ በሚዞሩ* ሰዎች ላይ ነው።

      31 በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣

      እየጣፈጠም ሲወርድ በወይን ጠጅ ቅላት ዓይንህ አይማረክ፤

      32 በመጨረሻ እንደ እባብ ይናደፋልና፤

      እንደ እፉኝትም መርዙን ይረጫል።

      33 ዓይኖችህ እንግዳ ነገር ያያሉ፤

      ልብህም ጠማማ ነገር ይናገራል።+

      34 በባሕር መካከል እንደተኛ፣

      በመርከብ ምሰሶም ጫፍ ላይ እንደተጋደመ ሰው ትሆናለህ።

      35 እንዲህ ትላለህ፦ “መቱኝ፤ ሆኖም አልተሰማኝም።*

      ደበደቡኝ፤ ሆኖም አልታወቀኝም።

      ተጨማሪ መጠጥ እጠጣ ዘንድ*

      የምነቃው መቼ ነው?”+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ