14 አርዘ ሊባኖስ የሚቆርጥ ሰው አለ።
እሱም አንድ የዛፍ ዝርያ ይኸውም የባሉጥ ዛፍ ይመርጣል፤
እስኪጠነክርለት ድረስ በጫካው ውስጥ ባሉት ዛፎች መካከል ይተወዋል።+
የላውሮ ዛፍ ይተክላል፤ ዝናብም ያሳድገዋል።
15 ከዚያም ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል።
የተወሰነውን እንጨት ወስዶ በማንደድ እሳት ይሞቃል፤
እሳት አያይዞም ዳቦ ይጋግራል።
ይሁንና አምላክ ሠርቶም ያመልከዋል።
የተቀረጸ ምስል ሠርቶበት በፊቱ ይደፋል።+