ኢሳይያስ 11:16 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 16 እስራኤል ከግብፅ ምድር በወጣበት ጊዜ እንደሆነው ሁሉ፣ከሕዝቡ የተረፉት ቀሪዎችም+ ከአሦር የሚወጡበት ጎዳና+ ይኖራል። ኢሳይያስ 35:8 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 8 በዚያም አውራ ጎዳና ይኖራል፤+ደግሞም “የቅድስና ጎዳና” ተብሎ ይጠራል። ንጹሕ ያልሆነ ሰው አይጓዝበትም።+ ጎዳናው፣ በመንገዱ ላይ ለሚሄዱት ብቻ ይሆናል፤ሞኞችም አይሄዱበትም። ኢሳይያስ 40:3 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 3 አንድ ሰው በምድረ በዳ እንዲህ ብሎ ይጮኻል፦ “የይሖዋን መንገድ ጥረጉ!*+ በበረሃ ለአምላካችን አውራ ጎዳናውን+ አቅኑ።+
8 በዚያም አውራ ጎዳና ይኖራል፤+ደግሞም “የቅድስና ጎዳና” ተብሎ ይጠራል። ንጹሕ ያልሆነ ሰው አይጓዝበትም።+ ጎዳናው፣ በመንገዱ ላይ ለሚሄዱት ብቻ ይሆናል፤ሞኞችም አይሄዱበትም።