-
2 ነገሥት 19:22-24አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
22 ያቃለልከውና የሰደብከው ማንን ነው?+
ድምፅህን ከፍ ያደረግከው፣+
እብሪተኛ ዓይንህንም ያነሳኸው በማን ላይ ነው?
በእስራኤል ቅዱስ ላይ እኮ ነው!+
23 በመልእክተኞችህ+ በኩል ይሖዋን አቃለሃል፤+ እንዲህም ብለሃል፦
‘ብዛት ባላቸው የጦር ሠረገሎቼ፣
ወደ ተራሮች ከፍታ፣
ርቀው ወደሚገኙትም የሊባኖስ ስፍራዎች እወጣለሁ።
ረጃጅሞቹን አርዘ ሊባኖሶች፣ ምርጥ የሆኑትንም የጥድ ዛፎች እቆርጣለሁ።
ርቆ ወደሚገኘው ማረፊያ ቦታ፣ በጣም ጥቅጥቅ ወዳለው ጫካ እገባለሁ።
24 ጉድጓድ ቆፍሬ የባዕድ አገር ውኃዎችን እጠጣለሁ፤
የግብፅንም ጅረቶች* ሁሉ በእግሬ ረግጬ አደርቃለሁ።’
-
-
ኢሳይያስ 10:20አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
20 በዚያ ቀን ከእስራኤላውያን መካከል የሚቀሩት፣
ከያዕቆብም ቤት የሚተርፉት ሰዎች
ከእንግዲህ ወዲህ፣ በመታቸው ላይ ፈጽሞ አይታመኑም፤+
ከዚህ ይልቅ የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይ
በታማኝነት ይደገፋሉ።
-