የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፀአት 15:11
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 ይሖዋ ሆይ፣ ከአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ ማን ነው?+

      በቅድስናው ኃያል መሆኑን የሚያሳይ እንደ አንተ ያለ ማን ነው?+

      በመዝሙር ልትወደስ የሚገባህ የምትፈራ አምላክ ነህ፤ ድንቅ ነገሮችን ታደርጋለህ።+

  • 2 ነገሥት 19:22-24
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 22 ያቃለልከውና የሰደብከው ማንን ነው?+

      ድምፅህን ከፍ ያደረግከው፣+

      እብሪተኛ ዓይንህንም ያነሳኸው በማን ላይ ነው?

      በእስራኤል ቅዱስ ላይ እኮ ነው!+

      23 በመልእክተኞችህ+ በኩል ይሖዋን አቃለሃል፤+ እንዲህም ብለሃል፦

      ‘ብዛት ባላቸው የጦር ሠረገሎቼ፣

      ወደ ተራሮች ከፍታ፣

      ርቀው ወደሚገኙትም የሊባኖስ ስፍራዎች እወጣለሁ።

      ረጃጅሞቹን አርዘ ሊባኖሶች፣ ምርጥ የሆኑትንም የጥድ ዛፎች እቆርጣለሁ።

      ርቆ ወደሚገኘው ማረፊያ ቦታ፣ በጣም ጥቅጥቅ ወዳለው ጫካ እገባለሁ።

      24 ጉድጓድ ቆፍሬ የባዕድ አገር ውኃዎችን እጠጣለሁ፤

      የግብፅንም ጅረቶች* ሁሉ በእግሬ ረግጬ አደርቃለሁ።’

  • ኢሳይያስ 10:20
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 20 በዚያ ቀን ከእስራኤላውያን መካከል የሚቀሩት፣

      ከያዕቆብም ቤት የሚተርፉት ሰዎች

      ከእንግዲህ ወዲህ፣ በመታቸው ላይ ፈጽሞ አይታመኑም፤+

      ከዚህ ይልቅ የእስራኤል ቅዱስ በሆነው በይሖዋ ላይ

      በታማኝነት ይደገፋሉ።

  • ሕዝቅኤል 39:7
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 7 ቅዱስ ስሜ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል እንዲታወቅ አደርጋለሁ፤ ከእንግዲህ ቅዱስ ስሜ እንዲረክስ አልፈቅድም፤ ብሔራትም እኔ ይሖዋ፣ የእስራኤል ቅዱስ+ እንደሆንኩ ያውቃሉ።’+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ