የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤርምያስ 4:10
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 10 ከዚያም እንዲህ አልኩ፦ “ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ ወዮ! ሰይፍ አንገታችን ላይ ተጋድሞ* እያለ ‘ሰላም ታገኛላችሁ’+ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ፈጽሞ አታለሃል።”+

  • ኤርምያስ 5:31
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 31 ነቢያቱ የሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤+

      ካህናቱም በራሳቸው ሥልጣን በኃይል ይገዛሉ።

      የገዛ ሕዝቤም ይህን ወዶታል።+

      ይሁንና መጨረሻው ሲመጣ ምን ታደርጉ ይሆን?”

  • ኤርምያስ 6:13, 14
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 13 “ከትንሹ አንስቶ እስከ ትልቁ ድረስ እያንዳንዱ አግባብ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ይሯሯጣል፤+

      ከነቢዩ አንስቶ እስከ ካህኑ ድረስ ሁሉም ያጭበረብራል።+

      14 ሰላም ሳይኖር፣

      ‘ሰላም ነው! ሰላም ነው!’ እያሉ

      የሕዝቤን ስብራት* ላይ ላዩን* ለመጠገን ይሞክራሉ።+

  • ኤርምያስ 23:16, 17
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 16 የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦

      “ትንቢት የሚተነብዩላችሁ ነቢያት የሚናገሩትን ቃል አትስሙ።+

      እነሱ እያሞኟችሁ ነው።*

      የሚናገሩት ራእይ ከይሖዋ አፍ የወጣ ሳይሆን+

      ከገዛ ልባቸው የመነጨ ነው።+

      17 እነሱ እኔን ለሚንቁ ሰዎች ደግመው ደጋግመው

      ‘ይሖዋ “ሰላም ታገኛላችሁ” ብሏል’ ይላሉ።+

      ግትር የሆነ ልባቸውን የሚከተሉትን ሁሉ

      ‘ጥፋት አይደርስባችሁም’ ይሏቸዋል።+

  • ኤርምያስ 27:8-10
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 8 “‘“‘የትኛውም ብሔር ወይም መንግሥት የባቢሎንን ንጉሥ ናቡከደነጾርን ለማገልገል ፈቃደኛ ባይሆን እንዲሁም አንገቱን በባቢሎን ንጉሥ ቀንበር ሥር ለማስገባት እንቢተኛ ቢሆን ያንን ብሔር በእሱ እጅ ፈጽሞ እስካጠፋው ድረስ በሰይፍ፣+ በረሃብና በቸነፈር* እቀጣዋለሁ’ ይላል ይሖዋ።

      9 “‘“‘ስለዚህ “የባቢሎንን ንጉሥ አታገለግሉም” የሚሏችሁን በመካከላችሁ ያሉትን ነቢያት፣ ሟርተኞች፣ ሕልም አላሚዎች፣ አስማተኞችና መተተኞች አትስሙ። 10 የሚተነብዩላችሁ ነገር ሐሰት ነውና፤ እነሱን የምትሰሙ ከሆነ ከምድራችሁ ተፈናቅላችሁ ወደ ሩቅ ቦታ ትወሰዳላችሁ፤ እኔም እበትናችኋለሁ፤ እናንተም ትጠፋላችሁ።

  • ሕዝቅኤል 13:10
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 10 ይህ ሁሉ የሚሆነው ሰላም ሳይኖር “ሰላም አለ!” እያሉ ሕዝቤን በማሳታቸው ነው።+ ሕዝቡ ጥንካሬ የሌለው ግድግዳ ሲሠራ እነሱ በኖራ ይለስኑታል።’*+

  • ሚክያስ 3:11
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 መሪዎቿ* በጉቦ ይፈርዳሉ፤+

      ካህናቷ በክፍያ ያስተምራሉ፤+

      ነቢያቷም በገንዘብ* ያሟርታሉ።+

      ያም ሆኖ “ይሖዋ ከእኛ ጋር አይደለም?+

      ምንም ዓይነት ጥፋት አይደርስብንም”+

      እያሉ በይሖዋ ይመካሉ።*

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ