9 ይሁን እንጂ ፅልማሞቱ ምድሪቱ በተጨነቀችበት ጊዜ እንደነበረው ይኸውም የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር በተዋረዱበት ወቅት እንደነበረው እንደቀድሞው ዘመን አይሆንም።+ በኋለኛው ዘመን ግን ምድሩ ማለትም በባሕሩ አጠገብ የሚያልፈው መንገድ፣ በዮርዳኖስ ክልል የሚገኘው የአሕዛብ ገሊላ እንዲከበር ያደርጋል።
2 በጨለማ ውስጥ ይሄዱ የነበሩ ሰዎች
ታላቅ ብርሃን አዩ።
ድቅድቅ ጨለማ ባጠላበት ምድር የሚኖሩ ሰዎችም
ብርሃን ወጣላቸው።+