ኢዩኤል
1 ወደ ፐቱኤል ልጅ፣ ወደ ኢዩኤል* የመጣው የይሖዋ ቃል ይህ ነው፦
2 “እናንተ ሽማግሌዎች ይህን ስሙ፤
የአገሪቱም* ነዋሪዎች ሁሉ ልብ በሉ።
በእናንተም ዘመን ይሁን በአባቶቻችሁ ዘመን
እንዲህ ያለ ነገር ተከስቶ ያውቃል?+
3 ይህን ለልጆቻችሁ ተናገሩ፤
ልጆቻችሁም ለልጆቻቸው፣
የእነሱ ልጆች ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ይናገሩ።
5 እናንተ ሰካራሞች ንቁ፤+ ደግሞም አልቅሱ!
እናንተ የወይን ጠጅ የምትጠጡ ሁሉ
ጣፋጩ የወይን ጠጅ ከአፋችሁ ላይ ስለተወሰደ ዋይ ዋይ በሉ።+
6 ኃያል የሆነና የሕዝቡ ብዛት ስፍር ቁጥር የሌለው ብሔር ምድሬን ወሮታልና።+
ጥርሶቹ የአንበሳ ጥርሶች ናቸው፤+ መንገጭላውም የአንበሳ መንገጭላ ነው።
7 የወይን ተክሌን አጠፋው፤ የበለስ ዛፌንም ጉቶ አደረገው፤
ቅርፊታቸውን ሙልጭ አድርጎ ልጦ ወዲያ ጣላቸው፤
በቅርንጫፎቻቸው ላይ አንድም ልጥ አልቀረም።
11 ገበሬዎች አፍረዋል፤ የወይን አትክልት ሠራተኞች ዋይ ዋይ ይላሉ፤
ይህም የሆነው ከስንዴውና ከገብሱ የተነሳ ነው፤
የእርሻው መከር ጠፍቷልና።
12 ወይኑ ደርቋል፤
የበለስ ዛፉም ጠውልጓል።
ሽማግሌዎቹንና የምድሪቱን ነዋሪዎች ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ ይሖዋ ቤት ሰብስቡ፤+
እርዳታም ለማግኘት ወደ ይሖዋ ጩኹ።
15 ከቀኑ የተነሳ ወዮላችሁ!
የይሖዋ ቀን ቀርቧልና፤+
ሁሉን ከሚችለው አምላክ ዘንድ እንደ ጥፋት ይመጣል!
16 ምግብ ከዓይናችን ፊት፣
ሐሴትና ደስታም ከአምላካችን ቤት ጠፍቶ የለም?
17 ዘሮቹ* ከአካፋዎቻቸው ሥር ጠውልገዋል።
ጎተራዎቹም ተራቁተዋል።
ጎታዎቹ* ፈራርሰዋል፤ እህሉ ደርቋልና።
18 መንጎቹ እንኳ ሳይቀሩ ያቃስታሉ!
ከብቶቹ ግራ ተጋብተው ይቅበዘበዛሉ፤ መሰማሪያ የላቸውምና!
የበጎቹም መንጋ ቅጣቱን ይቀበላል።
20 የዱር አራዊትም እንኳ አንተን በጉጉት ይጠባበቃሉ፤
ምክንያቱም የውኃ ጅረቶቹ ደርቀዋል፤
በምድረ በዳ ያለውን የግጦሽ መሬትም እሳት በልቶታል።”
2 “በጽዮን ቀንደ መለከት ንፉ!+
በቅዱሱ ተራራዬ ላይ ቀረርቶ አሰሙ።
ስፍር ቁጥር የሌለውና ኃያል የሆነ ሕዝብ ይመጣል፤+
ከዚህ በፊት እንደ እሱ ያለ ፈጽሞ ታይቶ አያውቅም፤
ወደፊትም ከትውልድ እስከ ትውልድ ድረስ
እንደ እሱ ያለ አይኖርም።
3 ከፊቱ ያለውን እሳት ይበላዋል፤
ከኋላው ያለውንም ነበልባል ያቃጥለዋል።+
4 መልካቸው እንደ ፈረስ መልክ ነው፤
እንደ ጦር ፈረሶችም ይጋልባሉ።+
5 በተራሮች አናት ላይ ሲዘሉ የሚሰማው ድምፅ እንደ ሠረገሎች ድምፅ፣+
ገለባንም እንደሚበላ የሚንጣጣ የእሳት ነበልባል ድምፅ ነው።
ለጦርነት እንደተሰለፈ+ ኃያል ሕዝብ ናቸው።
6 ከእነሱም የተነሳ ሕዝቦች ይጨነቃሉ።
የሰውም ፊት ሁሉ ይቀላል።
7 እንደ ተዋጊዎች በፍጥነት ጥቃት ይሰነዝራሉ፤
እንደ ወታደሮች ቅጥር ላይ ይወጣሉ፤
እያንዳንዱም የራሱን መንገድ ይዞ ይሄዳል፤
አቅጣጫቸውንም አይቀይሩም።
8 እርስ በርሳቸው አይገፋፉም፤
እያንዳንዱ ሰው መንገዱን ይዞ ይገሰግሳል።
አንዳንዶቹ በመሣሪያ* ተመተው ቢወድቁ እንኳ
ሌሎቹ አይፍረከረኩም።
9 ወደ ከተማዋ እየተጣደፉ ይገባሉ፤ በቅጥርም ላይ ይሮጣሉ።
ቤቶችም ላይ ይወጣሉ፤ እንደ ሌባ በመስኮት ይገባሉ።
10 ምድሪቱ በፊታቸው ትንቀጠቀጣለች፤ ሰማያትም ይናወጣሉ።
ፀሐይና ጨረቃ ጨልመዋል፤+
ከዋክብትም ብርሃናቸውን መስጠት አቁመዋል።
11 ይሖዋ በሠራዊቱ+ ፊት ድምፁን በኃይል ያሰማል፤ ሠራዊቱ ስፍር ቁጥር የለውም።+
ቃሉን የሚፈጽመው ኃያል ነውና፤
የይሖዋ ቀን ታላቅና እጅግ የሚያስፈራ ነው።+
ማንስ ሊቋቋመው ይችላል?”+
13 ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤+
ወደ አምላካችሁ ወደ ይሖዋም ተመለሱ፤
እሱ ሩኅሩኅና* መሐሪ፣ ለቁጣ የዘገየና+ ታማኝ ፍቅሩ የበዛ ነውና፤+
ሊያመጣ ያሰበውንም ጥፋት መለስ ብሎ ያጤናል።*
14 ደግሞም ተመልሶ ጉዳዩን እንደገና በማጤን፣*+
ለአምላካችሁ ለይሖዋ የእህል መባና የመጠጥ መባ ማቅረብ ትችሉ ዘንድ
በረከት ያስቀርላችሁ እንደሆነ ማን ያውቃል?
15 በጽዮን ቀንደ መለከት ንፉ!
16 ሕዝቡን ሰብስቡ፤ ጉባኤውን ቀድሱ።+
ሽማግሌዎቹን ሰብስቡ፤ ልጆቹንና ጡት የሚጠቡትን ሕፃናት ሰብስቡ።+
ሙሽራው ከውስጠኛው ክፍል፣ ሙሽሪትም ከጫጉላ ቤት ይውጡ።
17 የይሖዋ አገልጋዮች የሆኑት ካህናቱ
በበረንዳውና በመሠዊያው መካከል+ ሆነው ያልቅሱ፤ እንዲህም ይበሉ፦
‘ይሖዋ ሆይ፣ ለሕዝብህ እዘን፤
ርስትህ መሳለቂያ እንዲሆን አታድርግ፤
ብሔራትም አይግዟቸው።
ሕዝቦች “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?’+
18 ያን ጊዜ ይሖዋ ለምድሩ ይቀናል፤
ለሕዝቡም ይራራል።+
19 ይሖዋ ለሕዝቡ መልስ ይሰጣል፦
21 ምድር ሆይ፣ አትፍሪ።
ደስ ይበልሽ፤ ሐሴትም አድርጊ፤ ይሖዋ ታላላቅ ነገሮች ያደርጋልና።
23 እናንተ የጽዮን ልጆች ሆይ፣ በአምላካችሁ በይሖዋ ተደሰቱ፤ ሐሴትም አድርጉ፤+
እሱ የፊተኛውን ዝናብ በተገቢው መጠን ይሰጣችኋልና፤
በእናንተም ላይ ዝናቡን ያዘንባል፤
እንደቀድሞውም የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ ይሰጣችኋል።+
24 አውድማዎቹ በእህል ይሞላሉ፤
መጭመቂያዎቹም በአዲስ የወይን ጠጅና በዘይት ተሞልተው ያፈሳሉ።+
25 ደግሞም በመካከላችሁ የሰደድኩት ታላቁ ሠራዊቴ
ይኸውም የአንበጣ መንጋው፣ ኩብኩባው፣ የማይጠግበው አንበጣና አውዳሚው አንበጣ
ሰብላችሁን ለበሉባቸው ዓመታት ማካካሻ እሰጣችኋለሁ።+
ሕዝቤ ከእንግዲህ ወዲህ ፈጽሞ አያፍርም።
28 ከዚያ በኋላ በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ መንፈሴን አፈሳለሁ፤+
ወንዶች ልጆቻችሁና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፤
ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ፤
ወጣቶቻችሁም ራእዮችን ያያሉ።+
29 በዚያ ቀን በወንዶች ባሪያዎቼና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ሳይቀር
መንፈሴን አፈሳለሁ።
4 ጢሮስ፣ ሲዶና እና የፍልስጤም ግዛቶች ሁሉ፣
ከእኔ ጋር ምን ጉዳይ አላችሁ?
ላደረግኩባችሁ ነገር ብድራት ልትመልሱልኝ ነው?
ብድራት የምትመልሱልኝ ከሆነ
ብድራታችሁን ወዲያውኑ፣ በፍጥነት በራሳችሁ ላይ እመልሳለሁ።+
5 ምክንያቱም እናንተ ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤+
እጅግ ምርጥ የሆነውን ውድ ንብረቴንም ወደ ቤተ መቅደሶቻችሁ አስገብታችኋል፤
6 ደግሞም ከምድራቸው ርቀው እንዲሄዱ ለማድረግ ስትሉ
የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ለግሪኮች ሸጣችሁ፤+
7 እነሆ፣ እነሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች እንዲመለሱ አነሳሳቸዋለሁ፤+
ብድራታችሁንም በራሳችሁ ላይ እመልሳለሁ።
9 በብሔራት መካከል ይህን አውጁ፦+
‘ለጦርነት ተዘጋጁ!* ኃያላን ሰዎችን አነሳሱ!
ወታደሮቹ ሁሉ ቀርበው ጥቃት ይሰንዝሩ!+
10 ማረሻችሁን ሰይፍ፣ ማጭዳችሁንም ጦር ለማድረግ ቀጥቅጡ።
ደካማው ሰው “እኔ ብርቱ ነኝ” ይበል።
11 እናንተ ዙሪያውን ያላችሁ ብሔራት ሁሉ፣ ኑና ተረዳዱ፤ አንድ ላይም ተሰብሰቡ!’”+
ይሖዋ ሆይ፣ ኃያላንህን* ወደዚያ ቦታ አውርድ።
13 መከሩ ስለደረሰ ማጭድ ስደዱ።
የወይን መጭመቂያው ስለሞላ ኑ፣ ወርዳችሁ እርገጡ።+
ማጠራቀሚያዎቹ ሞልተው አፍስሰዋል፤ ክፋታቸው እጅግ በዝቷልና።
15 ፀሐይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤
ከዋክብትም ብርሃናቸውን አይሰጡም።
16 ይሖዋም ከጽዮን እንደ አንበሳ ያገሳል፤
ከኢየሩሳሌም ድምፁን በኃይል ያሰማል።
17 እናንተም እኔ በተቀደሰው ተራራዬ+ በጽዮን የምኖር አምላካችሁ ይሖዋ እንደሆንኩ ታውቃላችሁ።
20 ይሁንና ይሁዳ ምንጊዜም፣
ኢየሩሳሌምም ከትውልድ እስከ ትውልድ የሰው መኖሪያ ትሆናለች።+
“ይሖዋ አምላክ ነው” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “የምድሪቱም።”
ወይም “ባሏ።”
ወይም “ወጣት ሴት።”
ቃል በቃል “ታጠቁ።”
ወይም “ደረታችሁን ምቱ።”
ቃል በቃል “ጾምን ቀድሱ።”
“የደረቁት በለሶች” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ከጎተራ አነስ ያለ የእህል ማስቀመጫ።
ወይም “የምድሪቱ።”
ወይም “በተወንጫፊ መሣሪያዎች።”
ወይም “ቸርና።”
ወይም “ሊያመጣ ባሰበውም ጥፋት ይጸጸታል።”
ወይም “በመጸጸት።”
ቃል በቃል “ጾምን ቀድሱ።”
ሙት ባሕርን ያመለክታል።
ሜድትራንያን ባሕርን ያመለክታል።
ወይም “ምልክቶች አሳያለሁ።”
“ይሖዋ ፈራጅ ነው” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ቃል በቃል “ጦርነትን ቀድሱ!”
ወይም “ይሖዋ ሆይ፣ ተዋጊዎችህን።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ባዕዳንም።”
“የግራር ዛፎች” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “ደረቅ ወንዝ።”
ወይም “የደም ዕዳቸውን።”