የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwbq ርዕስ 46
  • ዲያብሎስ በእርግጥ አለ?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዲያብሎስ በእርግጥ አለ?
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ንዑስ ርዕሶች
  • መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
  • ሌሎች የተሳሳቱ አመለካከቶች
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ijwbq ርዕስ 46

ዲያብሎስ በእርግጥ አለ?

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

አዎ፣ ዲያብሎስ በእርግጥ አለ። እሱ “የዚህ ዓለም ገዥ” ነው፤ ይህ መንፈሳዊ ፍጡር ክፉ በመሆን በአምላክ ላይ ዓምጿል። (ዮሐንስ 14:30፤ ኤፌሶን 6:11, 12) መጽሐፍ ቅዱስ የዲያብሎስን ማንነት እንድናውቅ የሚረዱንን የሚከተሉትን መጠሪያዎችና አገላለጾች ይጠቀማል፦

  • ሰይጣን ማለትም ተቃዋሚ።—ኢዮብ 1:6

  • ዲያብሎስ ማለትም ስም አጥፊ።—ራእይ 12:9

  • እባብ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አታላይ የሚል ትርጉም አለው።—2 ቆሮንቶስ 11:3

  • ፈታኝ።—ማቴዎስ 4:3

  • ውሸታም።—ዮሐንስ 8:44

የክፋት ሐሳብ ወይም የክፋት ባሕርይ አይደለም

አንዳንዶች ሰይጣን ዲያብሎስ የሚባለው በውስጣችን ያለ የክፋት ሐሳብ ወይም የክፋት ባሕርይ እንደሆነ ያምናሉ። ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ሰይጣን ከአምላክ ጋር እንደተነጋገረ ይገልጻል። አምላክ ፍጹም ስለሆነ በውስጡ ካለ የክፋት ባሕርይ ጋር ሊነጋገር አይችልም። (ዘዳግም 32:4፤ ኢዮብ 2:1-6) በተመሳሳይም ሰይጣን ምንም ኃጢአት የሌለበትን ኢየሱስን ፈትኖታል። (ማቴዎስ 4:8-10፤ 1 ዮሐንስ 3:5) ከዚህ በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው፣ ሰይጣን በእውን ያለ አካል እንጂ በሰውኛ የተገለጸ የክፋት ባሕርይ እንዳልሆነ ነው።

ብዙ ሰዎች ሰይጣን በእውን ያለ አካል መሆኑን አለማመናቸው ሊያስደንቀን ይገባል? በፍጹም፣ ምክንያቱም ሰይጣን ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የማታለያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀም መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። (2 ተሰሎንቄ 2:9, 10) ከሚጠቀምባቸው ውጤታማ ዘዴዎች መካከል አንዱ ደግሞ ሰዎች የእሱን መኖር እንዳያምኑ ማድረግ ነው።—2 ቆሮንቶስ 4:4

ሌሎች የተሳሳቱ አመለካከቶች

የተሳሳተ አመለካከት፦ አምላክ ሰዎችን ለመፈተን በሰይጣን ይጠቀማል።

እውነታ፦ ዲያብሎስ የአምላክ ጠላት እንጂ የአምላክ አገልጋይ አይደለም። ሰይጣን ዲያብሎስ አምላክን የሚያገለግሉ ሰዎችን የሚቃወም ከመሆኑም ሌላ በሐሰት ይከስሳቸዋል።​—1 ጴጥሮስ 5:8፤ ራእይ 12:10

    የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ