የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
ማስታወቂያ
አዲስ የገባ ቋንቋ፦ Romany (Meçkar)
  • ዛሬ

እሁድ፣ መስከረም 7

ገና ልጅ ሳለ የአባቱን የዳዊትን አምላክ መፈለግ ጀመረ።—2 ዜና 34:3

ንጉሥ ኢዮስያስ ይሖዋን መፈለግ የጀመረው ገና በአሥራዎቹ ዕድሜ እያለ ነው። ስለ ይሖዋ መማርና የእሱን ፈቃድ ማድረግ ይፈልግ ነበር። ያም ቢሆን፣ ለዚህ ወጣት ንጉሥ ሕይወት ቀላል አልነበረም። የሐሰት አምልኮ በተስፋፋበት ዘመን ከንጹሑ አምልኮ ጎን መቆም ነበረበት። ያደረገውም ይህንኑ ነው! ኢዮስያስ ገና 20 ዓመት ሳይሞላው በፊት የሐሰት አምልኮን ከይሁዳ ማስወገድ ጀመረ። (2 ዜና 34:1, 2) ገና ልጅ ብትሆንም እንኳ ይሖዋን በመፈለግና ስለ ባሕርያቱ በመማር የኢዮስያስን ምሳሌ መከተል ትችላለህ። እንዲህ ማድረግህ ራስህን ለእሱ ለመወሰን ያነሳሳሃል። ራስህን ለይሖዋ መወሰንህ በዕለት ተዕለት ሕይወትህ ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል? በ14 ዓመቱ የተጠመቀው ሉክ እንዲህ ብሏል፦ “ከአሁን ጀምሮ በሕይወቴ ውስጥ የይሖዋን አገልግሎት አስቀድማለሁ፤ እሱን ለማስደሰትም ጥረት አደርጋለሁ።” (ማር. 12:30) አንተም እንዲህ ማድረግ የምትፈልግ ከሆነ ትልቅ በረከት ታገኛለህ! w23.09 11 አን. 12-13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሰኞ፣ መስከረም 8

በመካከላችሁ በትጋት እየሠሩና በጌታ ሥራ አመራር እየሰጧችሁ ያሉትን [አክብሯቸው]።—1 ተሰ. 5:12

ሐዋርያው ጳውሎስ ይህን ደብዳቤ በጻፈበት ወቅት የተሰሎንቄ ጉባኤ ከተቋቋመ አንድ ዓመትም አልሞላውም ነበር። በመሆኑም በዚያ ጉባኤ የነበሩት የተሾሙ ወንዶች ተሞክሮ ስለሚጎድላቸው አንዳንድ ስህተቶችን ሠርተው ሊሆን ይችላል። ያም ቢሆን አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባ ነበር። ታላቁ መከራ እየተቃረበ ሲመጣ ከዋናው መሥሪያ ቤትም ሆነ ከቅርንጫፍ ቢሮው መመሪያ ማግኘት አንችል ይሆናል፤ ስለዚህ በዚያ ወቅት ከአሁኑ ይበልጥ መመሪያ የምናገኝበት ዋነኛ መስመር ሽማግሌዎቻችን ሊሆኑ ይችላሉ። በመሆኑም ከአሁኑ ለሽማግሌዎቻችን ፍቅርና አክብሮት ማዳበራችን አስፈላጊ ነው። ምንም ነገር ቢመጣ የማስተዋል ስሜታችንን እንጠብቅ፤ በእነዚህ ታማኝ ወንድሞች አለፍጽምና ላይ ሳይሆን ይሖዋ በክርስቶስ አማካኝነት እየመራቸው በመሆኑ ላይ ትኩረት እናድርግ። የራስ ቁር የአንድን ወታደር ጭንቅላት እንደሚጠብቅለት ሁሉ የመዳን ተስፋችንም አስተሳሰባችንን ይጠብቅልናል። ይህ ዓለም የሚያቀርብልን ማንኛውም ነገር ከንቱ እንደሆነ እንገነዘባለን። (ፊልጵ. 3:8) ተስፋችን እንድንረጋጋና ሚዛናችንን እንድንጠብቅ ይረዳናል። w23.06 11-12 አን. 11-12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ማክሰኞ፣ መስከረም 9

ማስተዋል የጎደላት ሴት ጯኺ ናት። እሷ ጨርሶ ማመዛዘን አትችልም።—ምሳሌ 9:13

“ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበውን ግብዣ የሚሰሙ ሰዎች ግብዣዋን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል መወሰን ይኖርባቸዋል። ከፆታ ብልግና ለመራቅ የሚያነሳሱን አጥጋቢ ምክንያቶች አሉን። የምሳሌ መጽሐፍ፣ “ማስተዋል የጎደላት ሴት” “የተሰረቀ ውኃ ይጣፍጣል” እንደምትል ይናገራል። (ምሳሌ 9:17) “የተሰረቀ ውኃ” የሚለው አገላለጽ ምን ያመለክታል? መጽሐፍ ቅዱስ በትዳር አጋሮች መካከል የሚፈጸምን የፆታ ግንኙነት አርኪ ከሆነ ውኃ ጋር ያመሳስለዋል። (ምሳሌ 5:15-18) ሕጋዊ ጋብቻ የፈጸሙ ባለትዳሮች በፆታ ግንኙነት መደሰት ይችላሉ። ‘ከተሰረቀ ውኃ’ ጋር በተያያዘ ግን ሁኔታው በእጅጉ የተለየ ነው። ይህ አገላለጽ ያልተፈቀደ ወይም ከሥነ ምግባር ውጭ የሆነ የፆታ ግንኙነትን ሊያመለክት ይችላል። ሌቦች ብዙውን ጊዜ የሚሰርቁት ተደብቀው እንደሆነ ሁሉ ብዙዎች እንዲህ ያሉ ድርጊቶችን የሚፈጽሙት በድብቅ ነው። በተለይ ኃጢአት የሚፈጽሙት ሰዎች ድርጊታቸው ካልታወቀባቸው ደግሞ ‘የተሰረቀው ውኃ’ ይበልጥ ጣፋጭ መስሎ ሊታያቸው ይችላል። በዚህ መልኩ መታለላቸው እንዴት ያሳዝናል! ይሖዋ ሁሉንም ነገር ይመለከታል። የእሱን ሞገስ ማጣት ከምንም በላይ መራራ ነው፤ ስለዚህ የእሱን ሞገስ የሚያሳጣ ነገር ፈጽሞ ‘ጣፋጭ’ ሊሆን አይችልም።—1 ቆሮ. 6:9, 10፤ w23.06 22 አን. 7-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ