የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w13 11/1 ገጽ 5
  • ውሸት 2 ስለ አምላክ ማወቅ አይቻልም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ውሸት 2 ስለ አምላክ ማወቅ አይቻልም
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ለሥላሴ የሚሰጠው ማብራሪያ ምን ዓይነት ነው?
    በሥላሴ ማመን ይገባሃልን?
  • ክፍል 1 ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ የሥላሴን መሠረተ ትምህርት አስተምረዋልን?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
  • ሥላሴ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ነውን?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • ልታምንበት ይገባሃልን?
    በሥላሴ ማመን ይገባሃልን?
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
w13 11/1 ገጽ 5
[በገጽ 5 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | አምላክን መውደድ ከባድ እንዲሆን ያደረጉ ውሸቶች

ውሸት 2 ስለ አምላክ ማወቅ አይቻልም

ብዙዎች ምን ብለው ያምናሉ?

የክርስትና ሃይማኖት “ሦስቱ ዋና ዋና ክፍሎች ይኸውም የሮም ካቶሊክ፣ ምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ እንዲሁም ፕሮቴስታንት አምላክ አንድም ሦስትም እንደሆነ ያምናሉ፤ በሌላ አባባል አምላክን እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ብለው ይገልጹታል። በክርስትና ሃይማኖታዊ ትምህርት መሠረት፣ ይህ ሦስት አማልክት እንዳሉ የሚገልጽ ሳይሆን ሦስቱም አንድ እንደሆኑ የሚጠቁም ነው።”—ዘ ኒው ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው እውነት

የአምላክ ልጅ የሆነው ኢየሱስ፣ ከአባቱ ጋር እኩል እንደሆነ ወይም በመለኮት አንድ እንደሆኑ በፍጹም ተናግሮ አያውቅም። ከዚህ ይልቅ እንዲህ ብሏል፦ “የምትወዱኝ ቢሆን ኖሮ ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር፤ ምክንያቱም አብ ከእኔ ይበልጣል።” (ዮሐንስ 14:28) በተጨማሪም ከተከታዮቹ ለአንዷ “ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ፣ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ላርግ ነው” ብሎ ነግሯታል።—ዮሐንስ 20:17

መንፈስ ቅዱስ አካል አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ፣ የቀድሞ ክርስቲያኖች “በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ” ይላል፤ ይሖዋም “መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ” ብሏል። (የሐዋርያት ሥራ 2:1-4, 17) ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ ክፍል አይደለም። ከዚህ ይልቅ በሥራ ላይ የዋለ የአምላክ ኃይል ነው።

ይህን ማወቅ ለምን አስፈለገ?

የካቶሊክ ምሁራን የሆኑት ካርል ራነ እና ኸርበርት ፎርግሪምለ እንደገለጹት የሥላሴን ትምህርት “አንድ ሰው ራእይ ካልተገለጠለት በቀር ሊረዳው አይችልም፤ ራእይ ቢታየውም እንኳ ሙሉ በሙሉ ሊገነዘበው አይችልም።” ታዲያ ልታውቀው የማትችለውን አካል ልትወደው ትችላለህ? ከዚህ አንጻር የሥላሴ መሠረተ ትምህርት አምላክን እንዳናውቀውና እሱን እንዳንወድደው እንቅፋት ይሆንብናል ማለት ይቻላል።

ቀደም ባለ ርዕስ ላይ የተጠቀሰው ማርኮ፣ የሥላሴ መሠረተ ትምህርት አምላክን እንዳያውቅ እንቅፋት እንደሆነበት ተሰምቶት ነበር። እንዲህ ብሏል፦ “አምላክ ማንነቱን እንደደበቀኝ ተሰምቶኝ ነበር፤ ይህ ደግሞ ሊቀረብ እንደማይችልና ሚስጥራዊ እንደሆነ እንዳስብ አደረገኝ።” ይሁን እንጂ “አምላክ ግራ የሚያጋባ አምላክ አይደለም።” (1 ቆሮንቶስ 14:33 አሜሪካን ስታንዳርድ ቨርዥን) አምላክ ማንነቱን አልደበቀንም። እንዲያውም እንድናውቀው ይፈልጋል። ኢየሱስ “የምናውቀውን እናመልካለን” ብሏል።—ዮሐንስ 4:22

ማርኮ “አምላክ ሥላሴ እንዳልሆነ ሳውቅ ከእሱ ጋር የቀረበ ዝምድና መመሥረት ቻልኩ” ብሏል። ይሖዋን፣ ማንነቱ በግልጽ ሊታወቅ እንደሚችል አካል አድርገን የምንመለከተው ከሆነ እሱን መውደድ ከባድ አይሆንብንም። መጽሐፍ ቅዱስ “ፍቅር የማያሳይ አምላክን አያውቅም፤ ምክንያቱም አምላክ ፍቅር ነው” ይላል።—1 ዮሐንስ 4:8

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ