የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 9/96 ገጽ 5
  • መንግሥቱን ስበኩ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • መንግሥቱን ስበኩ
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—1996
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የመንግሥቱን ተስፋ ለሌሎች እንናገራለን
    የመንግሥት አገልግሎታችን—2007
  • ‘መልካም ዜና ማብሰር’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • አዎንታዊና የምታበረታታ ሁን
    በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ከሚሰጠው ሥልጠና ተጠቀም
  • አገልግሎትህን በተሟላ ሁኔታ እየፈጸምክ ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—1996
km 9/96 ገጽ 5

መንግሥቱን ስበኩ

1 በዕብራውያን 10:23 ላይ ‘የተስፋችንን ምሥክርነት አጥብቀን እንድንይዝ’ ተመክረናል። ተስፋችን ያተኮረው ደግሞ በአምላክ መንግሥት ላይ ነው። ኢየሱስ የመንግሥቱ ምሥራች ለአሕዛብ ሁሉ ሊሰበክ ይገባል ሲል ቀጥተኛ ትእዛዝ ሰጥቷል። (ማር. 13:10) በአገልግሎት በምንሠማራበት ጊዜ ይህንን መዘንጋት የለብንም።

2 ከሰዎች ጋር ስንገናኝ ፍላጎታቸውን የሚቀሰቅስ ወይም አንድ የሚያሳስባቸውን ነገር በመግለጽ ውይይት ለመጀመር እንሞክራለን። ብዙውን ጊዜ የምንጠቅሰው እነርሱም ጭምር የሚያውቋቸውን ነገሮች ሲሆን ከእነዚህም መካከል በአካባቢው የተፈጸመ ወንጀል፣ የወጣቶች ችግር፣ የዕለት ጉርስና ልብስ ለማግኘት ያለው ጭንቀት ወይም በዓለም መድረክ የታየ አንድ ችግርና እነዚህን የመሳሰሉ ነገሮች ይገኙበታል። የብዙዎቹ ሰዎች ልብ ያተኮረው በእነዚህ ‘የኑሮ ሐሳቦች’ ላይ ስለሆነ ብዙውን ጊዜ ጉዳዩ እንደሚያሳስበን ወይም ችግሩ እንደሚገባን ሆነን ስንቀርብ ብዙውን ጊዜ በልባቸው ያለውን ይነግሩናል። (ሉቃስ 21:34) ይህም ተስፋችንን ለማካፈል በር ሊከፍትልን ይችላል።

3 ይሁን እንጂ ካልተጠነቀቅን ውይይቱ አሉታዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ብቻ ያተኮረ ይሆንና ወደ ሰዎቹ የሄድንበትን ስለ መንግሥቱ መልእክት የመናገር ዓላማችንን ሳንፈጽም ልንቀር እንችላለን። ከፍተኛ ችግር ስላስከተሉት መጥፎ ሁኔታዎች ብንጠቅስም እንኳ ግባችን የሰው ልጆችን ችግሮች በሙሉ ጠራርጎ በሚያስወግደው መንግሥት ላይ እንዲያተኩሩ ማድረግ ነው። በእርግጥም ሁሉም ሰዎች ሊሰሙት የሚገባ ድንቅ ተስፋ አለን። በመሆኑም በመግቢያችን ላይ ስለ እነዚህ ‘አስጨናቂ ቀናት’ አንዳንድ ገጽታዎች ብንጠቃቅስም ወዲያው በዋናው መልእክታችን ማለትም ‘በዘላለሙ ወንጌል’ ላይ ማተኮር ይኖርብናል። በዚህ መንገድ አገልግሎታችንን ሙሉ በሙሉ ለመፈጸም እንችላለን።— 2 ጢሞ. 3:1፤ 4:5፤ ራእይ 14:6

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ