የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • g25 ቁጥር 1 ገጽ 10-11
  • በቃኝ በል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • በቃኝ በል
  • ንቁ!—2025
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
  • ምን ማድረግ ትችላለህ?
  • ባለህ ረክተህ የመኖርን “ሚስጥር” ተምረሃል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
  • ባለን ረክተን መኖር እንችላለን?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
  • በሕይወት እርካታ ለማግኘት የሚረዳ ቁልፍ
    ንቁ!—2021
  • መጣል በሚቀናው ኅብረተሰብ መካከል መኖር የሚያስከትለውን ፈታኝ ሁኔታ መቋቋም
    ንቁ!—2002
ለተጨማሪ መረጃ
ንቁ!—2025
g25 ቁጥር 1 ገጽ 10-11

የኑሮ ውድነትን መቋቋም

በቃኝ በል

በቃኝ የሚሉ ሰዎች ባሏቸው ነገሮች ይረካሉ። ሁኔታቸው ሲቀየር ደግሞ እንደ አቅማቸው ለመኖር ሲሉ ማስተካከያ ማድረግ አይከብዳቸውም።

አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

የሥነ ልቦና ባለሙያ የሆኑት ጄሲካ ኮለር እንደተናገሩት በቃኝ የሚሉ ሰዎች በጥቅሉ ሲታይ ለነገሮች አዎንታዊ አመለካከት አላቸው። በአብዛኛው ሲታይ በሌሎች አይቀኑም። ከዚህ አንጻር በቃኝ የሚሉ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ይበልጥ ደስተኛና ብዙም የማይጨነቁ መሆናቸው የሚያስገርም አይደለም። እንዲያውም በጣም ደስተኛ ከሚባሉት ሰዎች አንዳንዶቹ ብዙ ሀብት የላቸውም። እነዚህ ሰዎች በተለይ ደስተኛ ያደረጋቸው ገንዘብ ሊገዛቸው ለማይችላቸው ነገሮች ከፍተኛ ትኩረት መስጠታቸው ነው፤ ለምሳሌ ከቤተሰቦቻቸውና ከጓደኞቻቸው ጋር ጊዜ ማሳለፍ ያስደስታቸዋል።

“ምግብና ልብስ ካለን በእነዚህ ነገሮች ረክተን መኖር ይገባናል።”—1 ጢሞቴዎስ 6:8

ምን ማድረግ ትችላለህ?

ከሌሎች ጋር አትፎካከር። የአንተን ኑሮ ከሌሎች ቅንጡ የሚመስል ሕይወት ጋር ካወዳደርከው አንተ ያለህ ነገር ያንስብሃል፤ እንድትቀና ሊያደርግህም ይችላል። ከዚህ ባለፈ እንዲህ ያለው ንጽጽር እውነታውን የሚያንጸባርቅ ላይሆን ይችላል። አንዳንዶች ብዙ ንብረት ያላቸው ቢመስሉም በዕዳ ተዘፍቀው ሊሆን ይችላል። በሴኔጋል የምትኖረው ኒኮል እንዲህ ብላለች፦ “ደስተኛ ለመሆን ብዙ ነገሮች አያስፈልጉኝም። ሌሎች ከእኔ የበለጠ ነገር ቢኖራቸውም እንኳ ያለኝ ይበቃኛል የምል ከሆነ ደስተኛ እሆናለሁ።”

እንዲህ ለማድረግ ሞክር፦ የሌሎችን ሀብት ወይም ቅንጡ አኗኗር የሚያሳዩ ማስታወቂያዎችን ወይም ማኅበራዊ ሚዲያዎችን አትመልከት።

“አንድ ሰው ሀብታም ቢሆንም እንኳ ንብረቱ ሕይወት ሊያስገኝለት አይችልም።”—ሉቃስ 12:15


አመስጋኝ ሁን። በጥቅሉ ሲታይ አመስጋኝ የሆኑ ሰዎች ያላቸው ነገር እንደሚበቃቸው ይሰማቸዋል፤ ይህም ያም ያስፈልገኛል ወይም ይገባኛል ብለው አያስቡም። በሄይቲ የሚኖረው ሮቤርቶን እንዲህ ብሏል፦ “ሌሎች ለእኔና ለቤተሰቤ ስላሳዩን ደግነት ቆም ብዬ ለማሰብ እሞክራለሁ። ከዚያም ለሰዎቹ፣ ያደረጉልንን ነገር ምን ያህል እንደማደንቅ እነግራቸዋለሁ። የስምንት ዓመቱ ልጄም ለሚደረግለት ነገር ሁሉ ‘አመሰግናለሁ’ እንዲል አስተምሬዋለሁ።”

እንዲህ ለማድረግ ሞክር፦ በየቀኑ አመስጋኝ የሆንክባቸውን ነገሮች የመጻፍ ልማድ ይኑርህ። ለምሳሌ ጥሩ ጤንነትህን፣ ቤተሰብህን፣ ጓደኞችህን ሌላው ቀርቶ ፀሐይ ስትጠልቅ የሚፈጥረውን የሚያምር እይታ መጥቀስ ትችላለህ።

“ደስተኛ ልብ ያለው ሰው . . . ሁልጊዜ ግብዣ ላይ ያለ ያህል ነው።”—ምሳሌ 15:15

ሁላችንም በቃኝ ማለት ትግል የሚሆንብን ጊዜ አለ። እንዲህ ማድረጋችን ግን ይክሰናል! በቃኝ ለማለት መምረጥ ደስታን መምረጥ ነው፤ ደስታ ደግሞ ገንዘብ የማይገዛው ሌላ ባሕርይ ነው።

“ቤተሰባችን ባለው መርካትን ተምሯል፤ ይህም ትልቅ በረከት አስገኝቶልናል። ሕይወታችን ሩጫ የበዛበት አይደለም፤ አብረን የምናሳልፈው በቂ ጊዜ አለን፤ እንዲሁም ባሉን ነገሮች ተደስተን እንኖራለን።”—ኤሪክ፣ ዩናይትድ ስቴትስ

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ