የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 31
  • ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ሙሴ እና አሮን የአምላክን ቃል በድፍረት አውጀዋል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1996
  • ስድስቱ መቅሰፍቶች
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ይሖዋ ማን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 31

ምዕራፍ 31

ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት

ሙሴ ወደ ግብፅ ሲመለስ ለወንድሙ ለአሮን ስለተፈጸሙት ተአምራት ሁሉ ነገረው። ሙሴና አሮን እነዚህን ተአምራት ለእስራኤላውያን ሲያሳዩአቸው ሕዝቡ በሙሉ ይሖዋ ከእነርሱ ጋር እንደሆነ አመኑ።

ከዚያም ሙሴና አሮን ፈርዖንን ለማነጋገር ሄዱ። ‘የእስራኤል አምላክ ይሖዋ “ሕዝቤ ወደ ምድረ በዳ ሄደው ያመልኩኝ ዘንድ ሦስት ቀን ፍቀድላቸው” ብሏል’ ብለው ነገሩት። ይሁን እንጂ ፈርዖን ‘በይሖዋ አላምንም። እስራኤልንም አልለቅም’ ሲል መለሰ።

ሕዝቡ ከሥራ ነፃ ሆነው ይሖዋን ለማምለክ የሚችሉበት ጊዜ ለማግኘት ፈቃድ በመጠየቃቸው ፈርዖን ተቆጣ። በዚህም የተነሳ ከበፊቱ የበለጠ ከባድ ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው። እስራኤላውያን ይህ ችግር የደረሰብን በአንተ ምክንያት ነው ብለው በሙሴ ላይ አማረሩ፤ ሙሴም በጣም አዘነ። ይሖዋ ግን ምንም አትጨነቅ አለው። ‘ፈርዖን ሕዝቤን እንዲለቅ አደርገዋለሁ’ አለ።

ሙሴና አሮን ፈርዖንን እንደገና ለማነጋገር ሄዱ። በዚህ ጊዜ አንድ ተአምር ፈጸሙ። አሮን በትሩን ሲጥለው ትልቅ እባብ ሆነ። ይሁን እንጂ የፈርዖንም ጠቢባን በትሮቻቸውን ሲጥሉ በትሮቹ እባቦች ሆኑ። ግን ተመልከት! የአሮን እባብ የጠቢባኖቹን እባቦች እየበላቸው ነው። ያም ሆኖ ግን ፈርዖን እስራኤላውያንን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

ይሖዋ ፈርዖንን አንድ ትምህርት ሊያስተምረው ነው። ይህን ያደረገው እንዴት እንደሆነ ታውቃለህ? 10 መቅሠፍቶችን ወይም እጅግ አስከፊ የሆኑ ችግሮችን በግብፅ አገር ላይ በማምጣት ነው።

ብዙዎቹ መቅሰፍቶች ከደረሱ በኋላ ፈርዖን ወደ ሙሴ መልእክተኞችን ልኮ ‘መቅሰፍቱን አቁምልን፤ እስራኤልን እለቃለሁ’ አለው። ይሁን እንጂ መቅሰፍቱ ሲቆም ፈርዖን ሐሳቡን ለወጠ። ሕዝቡን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በመጨረሻ ከአሥረኛው መቅሰፍት በኋላ ፈርዖን እስራኤላውያንን ለቀቃቸው።

አሥሩ መቅሰፍቶች እያንዳንዳቸው ምን እንደሆኑ ታውቃለህ? ገጹን ግለጥና እነዚህ መቅሰፍቶች ምን እንደሆኑ እንመልከት።

ዘጸአት 4:​27-31፤ 5:​1-23፤ 6:​1-13, 26-30፤ 7:​1-13

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ