የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 20 ገጽ 52-ገጽ 53 አን. 3
  • ስድስቱ መቅሰፍቶች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ስድስቱ መቅሰፍቶች
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ይሖዋ ማን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • ‘ያህ ድነቴ ሆነልኝ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 20 ገጽ 52-ገጽ 53 አን. 3
የአንበጣ መንጋ

ትምህርት 20

ስድስቱ መቅሰፍቶች

ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄደው ‘ሕዝቤን የማትለቅ ከሆነ በግብፅ ላይ ተናካሽ ዝንብ አመጣለሁ’ በማለት አምላክ የተናገረውን መልእክት ነገሩት። ተናካሽ ዝንቦች የግብፃውያንን ቤቶች በሙሉ ወረሩ። አገሪቱ በሙሉ በተናካሽ ዝንቦች ተሞላች። እስራኤላውያን በሚኖሩበት በጎሸን ምድር ግን ምንም ተናካሽ ዝንብ አልነበረም። ከዚህኛው ማለትም ከአራተኛው መቅሰፍት ጀምሮ ያሉት መቅሰፍቶች የጎዱት ግብፃውያንን ብቻ ነው። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ‘እነዚህን ዝንቦች እንዲያስወግድልኝ ይሖዋን ለምኑልኝ። ሕዝቡን እለቃለሁ’ አላቸው። ሆኖም ይሖዋ ተናካሽ ዝንቦቹን ሲያስወግድላቸው ፈርዖን ሐሳቡን ቀየረ። ፈርዖን ከስህተቱ የሚማረው መቼ ይሆን?

ይሖዋም ‘ፈርዖን ሕዝቤን የማይለቅ ከሆነ የግብፃውያን እንስሳት ታመው ይሞታሉ’ አለ። በቀጣዩ ቀን እንስሳቱ መሞት ጀመሩ። የእስራኤላውያን እንስሳት ግን አልሞቱም። በዚህ ጊዜም ቢሆን ፈርዖን ሕዝቡን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

ከዚያም ይሖዋ ሙሴን አመድ ይዞ ወደ ፈርዖን በመሄድ አመዱን አየር ላይ እንዲበትነው ነገረው። አመዱ አቧራ ሆኖ አየሩን ሞላውና በግብፃውያኑ ሁሉ ላይ አረፈ። በዚህ የተነሳ በግብፃውያንና በእንስሶቻቸው ሁሉ ላይ የሚያም ቁስል ወጣ። ፈርዖን ግን አሁንም እስራኤላውያንን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

በግብፅ ላይ የደረሱት አራተኛ፣ አምስተኛና ስድስተኛ መቅሰፍቶች፦ ተናካሽ ዝንቦች፣ የእንስሳት መሞት፣ ቁስል

ይሖዋ ሙሴን ወደ ፈርዖን መልሶ በመላክ ይህን መልእክት እንዲነግረው አዘዘው፦ ‘አሁንም ሕዝቤን አትለቅም ማለት ነው? ነገ በምድሪቱ ላይ በረዶ ይዘንባል።’ በቀጣዩ ቀን ይሖዋ በረዶ፣ ነጎድጓድና እሳት ላከ። ከዚያ በፊት በግብፅ ላይ እንዲህ ያለ ኃይለኛ ዝናብ ዘንቦ አያውቅም። ዛፎቹና ተክሎቹ በሙሉ ወደሙ፤ በጎሸን ያሉት ተክሎች ግን ምንም አልሆኑም። ፈርዖንም ‘ይሖዋ ይህን እንዲያስቆምልኝ ለምኑልኝ! ከዚያ መሄድ ትችላላችሁ’ አለ። ሆኖም ልክ በረዶውና ዝናቡ እንዳቆመ ፈርዖን ሐሳቡን ቀየረ።

ከዚያም ሙሴ ‘ከበረዶው የተረፈውን ተክል አንበጦች ይበሉታል’ አለ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንበጦች መጥተው በእርሻውና በዛፎቹ ላይ የቀረውን በሙሉ በሉት። በዚህ ጊዜ ፈርዖን ‘ይሖዋ እነዚህን አንበጦች እንዲያስወግድልኝ ለምኑልኝ’ አለ። ፈርዖን ግን ይሖዋ አንበጦቹን ካስወገዳቸው በኋላም ሕዝቡን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

ይሖዋ ሙሴን ‘እጅህን ወደ ሰማይ ዘርጋ’ አለው። ወዲያውኑም ሰማዩ ሙሉ በሙሉ ጨለመ። ለሦስት ቀን ያህል ግብፃውያን ምንም ነገር ማየት አልቻሉም። እስራኤላውያን በሚኖሩበት አካባቢ ግን ብርሃን ነበር።

በግብፅ ላይ የደረሱት ሰባተኛ፣ ስምንተኛና ዘጠነኛ መቅሰፍቶች፦ በረዶ፣ አንበጦች፣ ጨለማ

ፈርዖን ሙሴን እንዲህ አለው፦ ‘አንተና ሕዝብህ መሄድ ትችላላችሁ። እንስሶቻችሁን ግን እዚሁ ትታችሁ ሂዱ።’ ሙሴም ‘ለአምላካችን መሥዋዕት አድርገን ስለምናቀርባቸው እንስሶቻችንን መውሰድ አለብን’ አለው። በዚህ ጊዜ ፈርዖን በጣም ተናደደ። ‘ከፊቴ ጥፋ! ከዚህ በኋላ አጠገቤ ብትደርስ እገድልሃለሁ’ በማለት ጮኸበት።

“እናንተም በጻድቁና በክፉው እንዲሁም አምላክን በሚያገለግለውና በማያገለግለው ሰው መካከል ያለውን ልዩነት ዳግመኛ ታያላችሁ።”—ሚልክያስ 3:18

ጥያቄ፦ ይሖዋ በመቀጠል የትኞቹን መቅሰፍቶች አመጣ? እነዚህ መቅሰፍቶች ከመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች የሚለዩት በምንድን ነው?

ዘፀአት 8:20–10:29

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ