የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 19 ገጽ 50-ገጽ 51 አን. 2
  • የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ስድስቱ መቅሰፍቶች
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ይሖዋ ማን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • ሙሴ እና አሮን የአምላክን ቃል በድፍረት አውጀዋል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1996
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 19 ገጽ 50-ገጽ 51 አን. 2
ሙሴና አሮን በፈርዖን ፊት ቆመው

ትምህርት 19

የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች

ግብፃውያን እስራኤላውያንን ባሪያ አድርገዋቸው ስለነበር የጉልበት ሥራ ያሠሯቸው ነበር። ይሖዋ ሙሴንና አሮንን ወደ ፈርዖን በመላክ ‘“ወደ ምድረ በዳ ሄደው እንዲያመልኩኝ ሕዝቤን ልቀቅ” ብላችሁ ንገሩት’ አላቸው። ፈርዖን ‘ይሖዋ የፈለገውን ቢል ግድ አይሰጠኝም፤ እስራኤላውያንን አለቅም’ በማለት በትዕቢት መለሰ። ከዚያም ፈርዖን የእስራኤላውያንን ሥራ የባሰ አከበደባቸው። ይሖዋ ግን ፈርዖንን አንድ ትልቅ ትምህርት ሊያስተምረው ነው። ይህን ያደረገው እንዴት እንደሆነ ታውቃለህ? በግብፅ ላይ አሥር መቅሰፍቶች በማምጣት ነው። ይሖዋ ሙሴን እንዲህ አለው፦ ‘ፈርዖን የእኔን ትእዛዝ አልሰማም። ጠዋት ላይ ወደ አባይ ወንዝ ይሄዳል። ስለዚህ ወደ እሱ ሂድና “ሕዝቤን አለቅም ስላልክ አባይ ውስጥ ያለው ውኃ በሙሉ ወደ ደም ይቀየራል” በለው።’ ሙሴ ይሖዋን በመታዘዝ ወደ ፈርዖን ሄደ። ፈርዖን እያየ አሮን የአባይን ወንዝ በዱላው ሲመታው ወንዙ ወደ ደም ተቀየረ። በዚህ ጊዜ ወንዙ መሽተት ጀመረ፤ ዓሦቹም ሞቱ፤ በዚህ የተነሳ ሕዝቡ ከአባይ ወንዝ መጠጣት አልቻለም። ፈርዖን ግን አሁንም እስራኤላውያንን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

ከሰባት ቀን በኋላ ይሖዋ ሙሴን እንደገና ወደ ፈርዖን በመላክ እንዲህ ብሎ እንዲነግረው አዘዘው፦ ‘ሕዝቤን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ካልሆንክ የግብፅ ምድር በሙሉ በእንቁራሪት ይሞላል።’ አሮንም ዱላውን አነሳ። ከዚያም እንቁራሪቶች ከውኃ እየወጡ ወደ ሰዎች ቤት ገቡ፤ ዕቃቸው ሁሉ በእንቁራሪት ተሞላ፤ አልጋቸውም ላይ ወጡ። ሁሉም ቦታ በእንቁራሪት ተሞልቶ ነበር! በዚህ ጊዜ ፈርዖን ሙሴን ‘ይህን መቅሰፍት እንዲያቆምልን ይሖዋን ለምንልን’ አለው። ፈርዖን እስራኤላውያንን እንደሚለቅ ቃል ገባ። ስለዚህ ይሖዋ መቅሰፍቱን አስቆመ፤ ግብፃውያኑም የሞቱትን እንቁራሪቶች ሰብስበው ከመሯቸው። ምድሪቱም መሽተት ጀመረች። ፈርዖን ግን አሁንም ሕዝቡን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

ከዚያም ይሖዋ ሙሴን ‘አሮን መሬቱን በዱላው ይምታው፤ ከዚያም አቧራው ወደ ትንኝ ይቀየራል’ አለው። ወዲያውኑ ምድሩ በሙሉ በትንኝ ተወረረ። የፈርዖን አገልጋዮች ራሳቸው ፈርዖንን ‘ይህ መቅሰፍት ከአምላክ የመጣ ነው’ አሉት። ፈርዖን ግን እስራኤላውያንን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆነም።

በግብፅ ላይ ከደረሱት አሥር መቅሰፍቶች መካከል ሦስቱ፦ የአባይ ወንዝ ወደ ደም መቀየር፣ እንቁራሪቶች እና ትንኞች

“ኃይሌንና ብርታቴን እንዲያውቁ አደርጋለሁ፤ እነሱም ስሜ ይሖዋ መሆኑን ያውቃሉ።”—ኤርምያስ 16:21

ጥያቄ፦ የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች የትኞቹ ናቸው? ይሖዋ እነዚህን መቅሰፍቶች ያመጣው ለምንድን ነው?

ዘፀአት 5:1-18፤ 7:8–8:19፤ ነህምያ 9:9, 10

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ