የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 21 ገጽ 54-ገጽ 55 አን. 1
  • አሥረኛው መቅሰፍት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አሥረኛው መቅሰፍት
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሙሴና አሮን ፈርዖንን አነጋገሩት
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ይሖዋ ማን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • አምላክ እስራኤላውያንን ነፃ አወጣቸው
    መጽሐፍ ቅዱስ—የያዘው መልእክት ምንድን ነው?
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 21 ገጽ 54-ገጽ 55 አን. 1
አንድ እስራኤላዊ የቤቱ መግቢያ ላይ ደም እየቀባ

ትምህርት 21

አሥረኛው መቅሰፍት

ሙሴ ወደ ፈርዖን ተመልሶ እንደማይመጣ ተናገረ። ሆኖም ከፈርዖን ፊት ከመውጣቱ በፊት እንዲህ አለው፦ ‘እኩለ ሌሊት ላይ ከፈርዖን ልጅ ጀምሮ እስከ ባሪያው ልጅ ድረስ በግብፅ ያለ የበኩር ልጅ በሙሉ ይሞታል።’

ይሖዋ ለእስራኤላውያን ልዩ ራት አዘጋጅተው እንዲበሉ ነገራቸው። እንዲህ አላቸው፦ ‘አንድ ዓመት የሆነው በግ ወይም ፍየል አርዳችሁ ደሙን የቤታችሁ መግቢያ ላይ ቀቡት። ሥጋውን ጥበሱና ካልቦካ ቂጣ ጋር ብሉት። ልብሳችሁን ለብሳችሁና ጫማችሁን አድርጋችሁ ለጉዞ ተዘጋጁ። በዚህ ሌሊት ነፃ አወጣችኋለሁ።’ እስራኤላውያን ምን ያህል ተደስተው ሊሆን እንደሚችል እስቲ አስበው።

እኩለ ሌሊት ላይ የይሖዋ መልአክ በግብፅ ወዳሉ ቤቶች በሙሉ ሄደ። መግቢያቸው ላይ ደም ባልተቀባባቸው ቤቶች ውስጥ ያሉት የበኩር ልጆች ሞቱ። ሆኖም መልአኩ ደም የተቀባባቸውን ቤቶች አልፎ ሄደ። በእያንዳንዱ የግብፃውያን ቤተሰብ ውስጥ ያለ የበኩር ልጅ ሁሉ ሞተ። ሆኖም ከእስራኤላውያን ልጆች መካከል አንዳቸውም አልሞቱም።

በዚህ ጊዜ የፈርዖን ልጅም ጭምር ሞተ። ፈርዖን ከዚህ በላይ ሊቋቋም አልቻለም። ወዲያውኑ ሙሴንና አሮንን ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ ‘ተነሱ። ከዚህ ውጡ። አምላካችሁን አምልኩ። እንስሶቻችሁንም ይዛችሁ ሂዱ!’

ጨረቃዋ ሙሉ ሆና ትታይ በነበረበት በዚያ ሌሊት እስራኤላውያን በቤተሰብና በነገድ ተከፋፍለው ከግብፅ ወጡ። በዚያ ጊዜ ከግብፅ የወጡት እስራኤላውያን ወንዶች 600,000 ሲሆኑ በርካታ ሴቶችና ልጆችም ነበሩ። በተጨማሪም ከእስራኤላውያን ጋር ይሖዋን ለማምለክ የመረጡ ሌሎች ብዙ ሰዎች አብረዋቸው ሄዱ። በመጨረሻ እስራኤላውያን ነፃ ወጡ!

እስራኤላውያን ይሖዋ እንዴት እንዳዳናቸው ማስታወስ እንዲችሉ በየዓመቱ ያንን ልዩ ራት እንዲመገቡ ትእዛዝ ተሰጣቸው። ይህ ልዩ ራት ፋሲካ ይባላል።

እስራኤላውያን ከግብፅ ሲወጡ

“በሕይወት ያቆየሁህ ኃይሌን በአንተ ለማሳየትና ስሜ በመላው ምድር እንዲታወጅ ለማድረግ ነው።”—ሮም 9:17

ጥያቄ፦ አሥረኛው መቅሰፍት ምን ነበር? እስራኤላውያን የበኩር ልጆቻቸው እንዳይገደሉ ከፈለጉ ምን ማድረግ ነበረባቸው?

ዘፀአት 11:1–12:42፤ 13:3-10

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ