መዝሙር 116
ደግነት ያለው ኃይል
በወረቀት የሚታተመው
1. አምላክ ሆይ፣ ከልብ እናወድስህ፤
ስለ ባሕርያትህ።
ታላቅ ቢሆንም ኃይልህ፣ ጥበብህ
ወደር የለው ደግነትህ።
2. ሸክም ከብዷቸው የደከሙትን
ልጅህ ጋብዟቸዋል።
ቀንበሩ ልዝብ፣ ሸክሙ ቀላል ነው፤
ማጽናኛ ከሱ ይገኛል።
3. አምላክንና ’የሱስን መምሰል፣
ፍላጎታችን ነው።
አዛኞችና ደጎች እንሁን፤
ደግነት ትልቅ ኃይል አለው።
(በተጨማሪም ሚክ. 6:8ን፣ ማቴ. 11:28-30ን፣ ቆላ. 3:12ን እና 1 ጴጥ. 2:3ን ተመልከት።)